ከ«የማርያም ቅዳሴ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
||
መስመር፡ 5፦ | መስመር፡ 5፦ | ||
ዘቅዱስ ሕርያቆስ |
ዘቅዱስ ሕርያቆስ |
||
}}</center> |
}}</center> |
||
'''አባ ሕርያቆስ ኤጲስ ቆጶስ''' አምላክን ስለ ወለደች ስለ <span style="color:red">እመቤታችን ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ </span> የደረሰው የቁርባን ምስጋና ይህ ነው ። |
|||
ልመናዋ በረከትዋ ከሁላችን ጋራ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን ። |
ልመናዋ በረከትዋ ከሁላችን ጋራ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን ። |
||
እትም በ01:07, 30 ኖቬምበር 2019
የማርያም ቅዳሴዘቅዱስ ሕርያቆስ |
---|
አባ ሕርያቆስ ኤጲስ ቆጶስ አምላክን ስለ ወለደች ስለ እመቤታችን ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ የደረሰው የቁርባን ምስጋና ይህ ነው ። ልመናዋ በረከትዋ ከሁላችን ጋራ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን ።
፩ ፤ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ። ከመንፈስህ ጋር አምላካችንን አመስግኑት ። እውነት ነው ይገባዋል ። ልቦናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ ። በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ አለን ።
፪ ፤ ልቦናዬ በጎ ነገርን አወጣ ።ልቦናዬ በጎ ነገርን አወጣ ። ልቦናዬ በጎ ነገርን አወጣ ።
፫ ፤ እኔም የማርያምን ቅዳሴ እናገራለሁ ። በማብዛት አይደለም በማሳነስ ነው እንጂ ። እኔም የድንግልን ውዳሴ እናገራለሁ ። መዘንጋት ባለበት ቃል በማስረዘም አይደለም ። በማሳጠር ነው እንጂ እኔም የድንግልን ገናንነትዋን እናገራለሁ ።
፬ ፤ ዛሬ በዚች ቀን በፍቅርና በትሕትና ግሩም በሚሆን ምሥጢር ፊት እቆማለሁ ። በዚህ ማዕድና ቁርባን ፊት ።
፭ ፤ መንፈሳቸውን ያረከሱ ሰዎች ከርሱ ሊቀምሱ የማይቻላቸው በእውነት ቁርባን ነው ። በበግ በጊደርና በላም ደም እንደ ነበረው እንደ ቀደሙት አባቶች መሥዋዕት አይደለም እሳት ነው እንጂ ።
፮ ፤ ፈቃዱን ለሚሠሩ ልቦናቸውን ላቀኑ ሰዎች የሚያድን እሳት ነው ። ስሙን ለሚክዱ ለዓመፀኞች ሰዎች የሚበላ እሳት ነው ።
ገፅ ፩