ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፪» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
Added links
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
መስመር፡ 2፦ መስመር፡ 2፦
|abovestyle=background:#BCD4E6
|abovestyle=background:#BCD4E6
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፪</span><div class=floatcenter>
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፪</span><div class=floatcenter>
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]]
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>

እትም በ04:13, 12 ኦክቶበር 2021

የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፪

ዘቅዱስ ሕርያቆስ


፸፯ ፤ እንዲህም እናምናለን እንዲህም እንታመናለን የሃይማኖትም ጸሎት እንበል ።
፸፰ ፤ ጸሎተ ሃይማኖት (የሃይማኖት ጸሎት) በል ።
፸፱ ፤ ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ ። ቅድስት ድንግልንም ለሁሉድንቅ የሚሆን የፅንሷን ነገር እንዲህ እያልን እንመርምራት ድንግል ሆይ እሳተ መለኮት በሆድሽ ባደረ ጊዜ ፊቱ እሳት ልብሱ እሳት ቀሚሱ እሳት ነው እንደምን አላቃጠለሽም ? ።
፹ ፤ ሰባት የእሳት ነበልባል መጋረጃ በሆድሽ ውስጥ ወዴት ተዘጋጀ ወዴትስ ተጋረደ ከጎንሽ በቀኝ ነውን ወይስ ከጎንሽ በግራ ነውን ትንሽ አካል ስትሆኚ ? ።
፹፩ ፤ የሚያንፀባርቅ ነደ እሳት የሚከበው ኪሩቤል የተሸከሙትን ዙፋን በሆድሽ ውስጥ በወዴት ተዘጋጀ ወዴትስ ተተከለ ታናሽ ሙሽራ ስትሆኚ ? ።
፹፪ ፤ ከአገልጋይነት ጋራ እናትነት እንደምን ያለ ነው ። ከስፋት ጋራ የሆድ መጥበብ እንደ ንብ ያለ ሩካቤ ከቃል ድምፅ የተገኘ ፅንስ ከድንግልና ጋር አንድ የሆነ ሐሊብ ።
፹፫ ፤ ይህንንም ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ የልጅሽን የባሕሩን ጥልቅነት ሊዋኝ ይወዳል የወዳጅሽ የመሠወሪያው ማዕበልም ያማታዋል ።
፹፬ ፤ ዳግመኛም ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ ተሠውሮ ወደላይ ወጥቶ የሕያው መሠወሪያ የሆነውን ሊገልጥ ይወዳል ። ከነደ እሳትነቱ የተነሣ ይፈራል ከዐየራት ከእርቧቸው እርቦ አይደርስም ።
፹፭ ፤ ይህንንም ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ በነፋስ ትከሻ ተጭኖ በምሥራቅና በምዕራብ በሰሜንና በደቡብ በዳርቻዎችም ሁሉ ሊበር ይወዳል ። የፍጡራንን አኗኗር ያይ ዘንድ የአብርሕትንም ጥልቅነታቸውን ይለካ ዘንድ የሰማይን ርዝመቱን ያውቅ ዘንድ በሁሉ ዘንድ በሁሉም ይዞራል ። አቅቶት ወደ ቀደመ አኗኗሩ ይመለሳል ።
፹፮ ፤ አሁንም ገናናነቱን እንመርምር ጥልቅነቱንም እንጠናቀቅ ። የገናናነቱንም መጠን ለማመስገን የነብያትና የሐዋርያት አንደበት የማይቻለው ነው ።
፹፯ ፤ የማይደፈር ግሩም ነው ። በኛ ዘንድ ግን ትሑት ነው ። የማይገኝ ልዑል ነው ። በኛ ዘንድ ግን አርአያ ግብርን ነሣ ። የማይዳሰስ እሳት ነው ። እኛ ግን አየነው ዳሰስነውም ከእርሱም ጋራ በላን ጠጣን ። አሁንም እንዲህ እያልን እናመስግነው ።
፹፰ ፤ ቅዱስ እግዚአብሔር እስከ መጨረሻው ።
፹፱ ፤ ድንግል ሆይ የሚበላውን ያፈራሽልን የሚጠጣውን ያስገኘሽልን ።
፺ ፤ ወዮ ካንቺ የተገኘ ኅብስት በማመን ከርሱ የሚቀበሉ ሕይወትንና ደኅንነት የሚሰጥ ነው ።
፺፩ ፤ ወዮ ካንቺ የተገኘ ኅብስት በማመን ከርሱ ለማይቀበሉ ሰዎች የማይላመጥ ጽኑ ነው ። ይኸውም ኃያል የሚሆን የአድማስ ድንጋይ ነው ።