ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፯» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Added links
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
 
መስመር፡ 4፦ መስመር፡ 4፦
|image=[[ስዕል:ሥጋወ ደሙ.jpeg]]
|image=[[ስዕል:ሥጋወ ደሙ.jpeg]]
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>
|data1=<span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>
}}</center>
}}</center>
<br>፴፯ ፤ <span style=color:red>ድንግል ሆይ </span>በኃጢያት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ ።
<br>፴፯ ፤ <span style=color:red>ድንግል ሆይ </span>በኃጢያት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ ።

በ07:02, 12 ኦክቶበር 2021 የታተመው ያሁኑኑ እትም

የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፯

ዘቅዱስ ሕርያቆስ


፴፯ ፤ ድንግል ሆይ በኃጢያት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ ።
፴፰ ፤ ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ ።
፴፱ ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለሽም ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ ።
፵ ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ ።
፵፩ ፤ ድንግል ሆይ ከአንቺ አስቀድሞ ከአንቺም በኋላ እንዳሉ ሴቶች እድፍ የምታውቂ አይደለሽም በንጽሕና በቅድስና ያጌጥሽ ነሽ እንጂ ።
፵፪ ፤ ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጎልማሶች ያረጋጉሽ አይደለሽም የሰማይ መላእክት ጎበኙሽ እንጂ ። እንደተነገረ ካህናትና የካህናት አለቆች አመሰገኑሽ እንጂ ።
፵፫ ፤ ድንግል ሆይ ለዮሴፍ የታጨሽ ለመገናኘት አይደለም ንጹሕ ሆኖ ሊጠብቅሽ ነው እንጂ ። እንዲሁ ስለሆነ ።
፵፬ ፤ እርሱ ቅሉ እግዚአብሔር አብ ንጽሕናሽን ባየ ጊዜ ስሙ ገብርኤል የሚባል ብርሃናዊ መልአኩን ወደ አንቺ ላከ ። መንፈስ ቅዱስ በላይሽ ይመጣል የልዑል ኃይልም ይጋርድልሻል አለሽ ።