ከ«ሀዲስ ዓለማየሁ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
No edit summary |
eratum |
||
መስመር፡ 1፦ | መስመር፡ 1፦ | ||
[[Image:Haddis_alemayehu.jpg|thumb|right]]ደራሲ '''ሐዲስ ዓለማየሁ''' ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በ[[ደብረ ማርቆስ]] አውራጃ በጎዛመን ወረዳ |
[[Image:Haddis_alemayehu.jpg|thumb|right]]ደራሲ '''ሐዲስ ዓለማየሁ''' ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በ[[ደብረ ማርቆስ]] አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንዳዶም ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በ[[ጥቅምት 5]] ቀን [[1903]] ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት መከታተል ጀመሩ። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ ኤልያስ፣ በደብረ ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ [[አዲስ አበባ]] በመሄድ በ[[ስዊድን]] ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ [[ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት]] ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ግዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት [[ጣሊያን]] ወረራ ተከሰተ። |
||
በጦር ሜዳ ዘምተው ሲዋጉ ቆይተው በአርበኝነት ሲንቀሳቀሱ በመያዛቸው ጣሊያን ከራስ [[እምሩ ኃይለ ሥላሴ]] ጋር ተልከው ለሰባት ዓመት በ[[ፖንዞ ደሴት]]ና በ[[ሊፓሪ ደሴት]] ታስረው ቆይተዋል። |
በጦር ሜዳ ዘምተው ሲዋጉ ቆይተው በአርበኝነት ሲንቀሳቀሱ በመያዛቸው ጣሊያን ከራስ [[እምሩ ኃይለ ሥላሴ]] ጋር ተልከው ለሰባት ዓመት በ[[ፖንዞ ደሴት]]ና በ[[ሊፓሪ ደሴት]] ታስረው ቆይተዋል። |
እትም በ13:43, 27 ማርች 2008
ደራሲ ሐዲስ ዓለማየሁ ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንዳዶም ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በጥቅምት 5 ቀን 1903 ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት መከታተል ጀመሩ። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ ኤልያስ፣ በደብረ ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ በስዊድን ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ግዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት ጣሊያን ወረራ ተከሰተ።
በጦር ሜዳ ዘምተው ሲዋጉ ቆይተው በአርበኝነት ሲንቀሳቀሱ በመያዛቸው ጣሊያን ከራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴ ጋር ተልከው ለሰባት ዓመት በፖንዞ ደሴትና በሊፓሪ ደሴት ታስረው ቆይተዋል።
ከዚያም የተባባሪ ኃያላት ወታደሮች በ1935 ዓ.ም. ሲያመልጧቸው በተመለሱበት ጊዜ በትምህርታቸው እንደገና በኦክስፎርድ ከገፉ በኋላ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት በተለይም በትምህርት ሚኒስቴር ለረጅም ግዜ አገልግለዋል።
- 1936 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኛ
- 1937-1938 - የኢትዮጵያ ቆንሱል በኢየሩሳሌም
- 1938 - በ International Telecommunications Conference አትላንቲክ ከተማ፣ ኒው ጄርዚ ወኪል
- 1938-1942 - በተባባሪ መንግሥታት ቢሮ ኒው ዮርክ ሠራተኛ
- 1942-1948 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይረክተርና ምክትል
- 1948-1952 - የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ አምባሰደር
- 1952 - የትምህርት ሚኒስትር
- 1952-1957 - የኢትዮጵያ አምባሰደር ወደ እንግሊዝና ሆላንድ
- 1957-1958 - የልማት ሚኒስትር
- 1960-1966 - ሴናቶር
ሐዲስ ዓለማየሁ በርካታ የስነጽሑፍ ሥራዋችን አበርክተዋል። ከነዚህም ውስጥ ታላቅ አድናቆትንና እውቅናን ያተረፈው ሥራቸው ፍቅር እስከ መቃብር (1958) በሁለት የተለያዩ መደቦች ውስጥ የሚገኙ የሁለት ሰዎች የፍቅር ታሪክ ላይ ሲያተኩር፤ በጊዜው የነበረውን ወግና ልማድ ይገልጻል። እንዲሁም በ1970 ወንጀለኛው ዳኛ በ 1980 ደግሞ ስለ ማህበራዊ ጉዳዮችና ስለ ጣሊያን ውርስ የሚዳስሰውን የልም እዣት የተሰኙትን ልብ ወለድ ታሪኮች ለንባብ አቅርባዋል።
ከዚህ ባሻገር:
- የአበሻና የወደኋላ ጋብቻ - ተውኔት
- ተረት ተረት የመሰረት
- ትዝታ
የተሰኙት ጽሁፎችና የሌሎች በርካታ ሥራዎች ባለቤት ናቸው።
ሐዲስ ዓለማየሁ በኢትዮጵያ የስነ ጽሑፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከታቸው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክቶርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል። ደራሲው በኅዳር 26 ቀን 1996 ዓ.ም. በ94 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ዋቢ መጻሕፍት
- Historical Dictionary of Ethiopia
- ብሔራዊ ቢብሎግራፊ (የደራሲያን አጭር የሕይወት ታሪክ)፤ (1998 ዓ.ም)ገጽ 13