ሐምሌ ፪

ከውክፔዲያ
(ከሐምሌ 2 የተዛወረ)

ሐምሌ ፪ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፪ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፷፬ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፷፫ ቀናት ይቀራሉ።

አቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፭፻፴፫ ዓ/ም - ኢትዮጵያን የወረረውን ግራኝ መሐመድን ለመከላከል የዘመተውን የ|ብርቱጋል ሠራዊት የመራው ኤስቴቫዎ ዳጋማ ወንድሙን ክሪስቶቫዎ ዳጋማ ን ከአራት መቶ ወታደሮችና መቶ ሃምሳ ባሪያዎች ጋር ትቶ ከምጽዋ ወደብ ወደአገሩ ተጓዘ።

፲፱፻፴፱ ዓ/ም - የእንግሊዝ ልዕልት፣ (አሁን ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ) እና የሌፍተናንት (አሁን የኤዲንበራ መስፍን ልዑል) ፊሊፕ የጋብቻ እጭት ይፋ ተደረገ።

፲፱፻፹፫ ዓ/ም - የደቡብ አፍሪቃ ሪፑብሊክ ለሠላሳ ዓመታት ከተገለለችበት የኦሊምፒክ ማሕበር ተመልሳ አባል ሆነች።

፲፱፻፺፬ ዓ/ም - የቀድሞውን የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የተካው የአፍሪቃ ኅብረት አዲስ አበባ ላይ ተመሠረተ። የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚደንት ጻቦ እምቤኪ የኅብረቱ የመጀመሪያው ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ።

ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፱፻፯ ዓ.ም - ስመ ጥሩው ኢትዮጵያዊ አርበኛ እና የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ሊቀ መንበር የነበሩት ክቡር ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን ቡልጋ፣ ልዩ ስሙ ቡሄ ዓምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ።

፲፱፻፰ ዓ/ም - ከ፲፱፻፷፫ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፷፯ ዓ/ም የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ሰር ኤድዋርድ ሂዝ

፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የቀድሞው የሞሮኮ ንጉሥዳግማዊ ሀሳን(አረብኛ: الحسن الثاني‎)። ንጉሡ የዛሬው የንጉሥ ሞሀመድ ራብእ (አረብኛ: محمد السادس‎) አባት ናቸው።

፲፱፻፴፬ ዓ/ም - ሪቻርድ ራውንድትሪ (Richard Roundtree). ሪቻርድ በዋና ተዋናይነት <<ጆን ሻፍት>> (John Shaft) ሆኖ <<ሻፍት ኢን አፍሪካ>> (Shaft in Africa) በተባለው ፊልም ላይ ከዘነበች ታደሰ (ሸርሙጣ ሆና) እና ደበበ እሸቱ (ዋሳ Wassa) ጋር ሠርቷል፡

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]



የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ