Jump to content

መሠረተ እና የበላይ መዋቅር

ከውክፔዲያ


በማርክሳዊ ርዕዮተ ዓለም መሠረት፣ የሰው ልጅ ኅብረተሰብ ሁለት ክፍሎች አሉት: መሠረተ እና የበላይ መዋቅር መሰረተ መዋቅሩ የምርት ኃይሎችንና የምርት ግንኙነቶችን—ማለትም የአሰሪና ሠራተኛ የሥራ ሁኔታዎች፣ የቴክኒክ የሥራ ክፍፍልና የባለቤትነት ግንኙነቶችን—ያጠቃልላል፤ ሰዎች ለመኖር አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችንና የቅንጦት ዕቃዎችን ለማምረት በእነዚህ ግንኙነቶች ውስጥ ይገባሉ። እነዚህ ግንኙነቶች የማህበረሰቡን ሌሎች ግንኙነቶችና አስተሳሰቦች ይወስናሉ፤ ይህ ደግሞ የበላይ መዋቅር ተብሎ ይጠራል። የማህበረሰቡ የበላይ መዋቅር ባህልን፣ ተቋማትን፣ የፖለቲካ ሥልጣን መዋቅሮችን፣ ማህበራዊ ሚናዎችን፣ ሥርዓቶችን እና መንግሥትን ያካትታል። መሰረተ መዋቅሩ የበላይ መዋቅሩን ይወስናል፤ ነገር ግን ግንኙነታቸው ሙሉ በሙሉ የምክንያትና ውጤት አይደለም። ምክንያቱም የበላይ መዋቅሩ ብዙውን ጊዜ በመሰረተ መዋቅሩ ላይ ተጽዕኖ ስለሚያሳድር ነው፤ ሆኖም የመሰረተ መዋቅሩ ተጽዕኖ የበለጠ ጉልህ ነው። በሌላ በኩል፣ ቀኖናዊ ማርክሲዝም የመሰረተ መዋቅሩና የበላይ መዋቅሩ ግንኙነት የአንድ አቅጣጫ ብቻ እንደሆነ ያምናል።።