መስቀል አደባባይ

ከውክፔዲያ
የመስቀል መስቀል አደባባይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የበዓል አደባባይ ነው

መስቀል አደባባይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪካዊ ይዞታ ነው በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ የሚገኝ አደባባይ ነው።‹‹መስቀል አደባባይ ለክብረ በዓል፣ የሚውል የአዲስ አበባ ከኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች "የመስቀል አምልኮ" አደባባይ ነው፤››[1]

ባለቤትነቱን እና ስያሜውን ያገኘው እምነት ተከታዮች በየዓመቱ በሚከበረው የ መስቀል በዓል ምክንያት ነው። ይህ ቦታ በደርግ አገዛዝ ዘመን በኦፊሴል "አብዮት አደባባይ" ተብሎ ይጠራ የነበረና በየዓመቱ የአብዮቱ ክብረ በዓል ይከናወንበት ነበር። በዚህ ወቅትም የጊዜው የደርግ መንግስት እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አለመግባባት ተፈጥሮ በየ ወቅቱ የሚጠየቅ ጉዳይ ነበር በወቅቱ የነበረው መንግስት ግን በአጠቃላይ ከሀይማኖት ጋር መልካም ግኑኝነት ስላልነበረው ጥያቄዎችን አልመለሰም ነበር። ከ1967 ዓ.ም. መገባደጃ ጀምሮ በዘመነ ደርግ ‹‹አብዮት አደባባይ›› ይባል ነበር፡፡ኢሕአዴግ መንበረ ሥልጣኑን ከያዘ በኋላ ከ1984 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ቀድሞው መጠሪያ መስቀል አደባባይ መመለሱ ይታወቃል፡፡ የጥናት ድርሳናት እንደሚያሳዩት መስቀል አደባባይ በ1950ዎቹ መጀመርያ ስያሜው ከማግኘቱ በፊት በእስጢፋኖስ አደባባይነት እንደሚታወቅ፣ [2]

  1. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2021-06-02. በ2021-05-30 የተወሰደ.
  2. ^ [1] Archived ጁን 2, 2021 at the Wayback Machine[2] Archived ጁን 2, 2021 at the Wayback Machine