Jump to content

መታሰቢያ ዮሴፍ

ከውክፔዲያ


ደራሲ እና የሚዲያ አንተርፕርነር
የተወለዱት ዋሽንግተን ዲሲ
ዜግነት ኢትዮ-አሜሪካዊ
ሀይማኖት ክርስትና

መታሰቢያ ዮሴፍ ኢትዮ-አሜሪካዊ የባህል ስትራቴጂስት፣ ደራሲ እና የሚዲያ አንተርፕርነር እንዲሁም በባህላዊ ስትራቴጂ እና በቬንቸር ዲዛይን ላይ ትኩረቱን አድርጎ በመላው አፍሪካ እና የአፍሪካ ዲያስፖራ ማሕበረሰብ ውስጥ የሚንቀሳቀስ የምክር እና የፈጠራ መድረክ የሆነው የአዲስ ፊውቸርስ ላብ የምርምር ድርጅት መስራች እና የማኔጅመንት አጋር ናት። መታሰቢያ የኢትዮጵያ ፈጠራ ኢኮኖሚ ፌስቲቫል የሆነው የዲዛይን ሳምንት: አዲስ አበባ መስራች በተጨማሪም በወጣቶች ላይ ትኩረቱን ያደረገ D!NK ቲቪ የተባለ ዲጂታል ሚዲያ ባለቤትም ጭምር ናት።

እድገትና እና ትምህርት

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መታሰቢያ በዋሽንግተን ዲሲ የተወለደች ሲሆን እ.ኤ.አ. በ2009 ዓ.ም ከሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ጥበብ ታሪክ የመጀመሪያ ዲግሪዋን እንዲሁም በ2013 ዓ.ም ከጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ በመገናኛ፣ ባህል እና ቴክኖሎጂ ሁለተኛ ዲግሪዋን አግኝታለች።[1][2]

የዲዛይን ሳምንት፣ አዲስ አበባ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እ.ኤ.አ. በ2015 መታሰቢያ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን አለም አቀፍ የዲዛይን ፌስቲቫል የሆነውን የዲዛይን ሳምንት: አዲስ አበባ ለፈጠራ ኢኮኖሚ ልማት እና ለአለም አቀፍ የባህል ልውውጥ ይውል ዘንድ አቋቁማለች። ባለፉት አስር አመታት ዝግጅቱ ከ100 በላይ ፕሮግራሞችን አስተናግዷል፣ ከ50,000 በላይ ተሳታፊዎችን ስቧል፣ እንዲሁም ከብሪቲሽ ካውንስል፣ ከአለም አቀፍ ኤምባሲዎች እና የልማት ተቋማት ጋር ትብብርን አመቻችቷል። በ2025 መታሰቢያ የበዓሉን አመራር ወደ አዲስ ቡድን ቀይራ እንደ አማካሪ በማገልገል ላይ ትገኛለች።[3][1][4]

የፋይናንስ ቴክኖሎጂ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እ.ኤ.አ ከ2016 እስከ 2018 ዓ.ም ፣ መታሰቢያ በኢትዮጵያ መሪ የፊንቴክ ኩባንያ በሆነው የክፍያ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ዋና የግብይት ኦፊሰር እና ከፍተኛ የንግድ ፈጠራ ሀላፊ ሆና አገልግላለች። ከማስተርካርድ ጋር በሽርክና የተገነባውን MELA የተባለውን ዓለም አቀፍ የሐዋላ አገልግሎት አበልጽጋለች እንዲሁም የየኔጉዞ የዲጂታል ትራንስፖርት ክፍያ ስርዓት ከመንግስት አጋሮች ጋር በመተባበር ተግባራዊ እንዲሆን አድርጋለች። የመንግስት እና የግል ኢኒሼቲቮችን በማቀናጀት እንዲሁም ከ5,000 በላይ ለሆኑ ሴቶች እና በገጠር ለሚኖሩ ባንክ የሌላቸው ማህበረሰቦች የዲጂታል ማካተት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ ለኢትዮጵያ የፊንቴክ ስነምህዳር እድገት ዕገዛ ማድረግ ችላለች።[5]

አዲስ ፊውቸርስ ላብ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እ.ኤ.አ. በ2018 ዓ.ም መታሰቢያ ምርምርን ፣የስትራቴጄክ የማማከር አገልግሎትን አና የቬንቸር ዲዛይን ከአገር በቀል ፈጠራዎች ጋር የሚያጣምር ድርጅት የሆነውን አዲስ ፊውቸርስ ላብ አቋቋመች። አዲስ ፊውቸርስ ላብ ትኩረቱን ያደረገው በአፍሪካ የባህል እና ኢኮኖሚ እድገት ላይ ትልቅ ተፅእኖ ባላቸው የሚዲያና መዝናኛየዘላቂ ውበት፣ የእርሻ ማቀነባበር፣ የባህል እውቀት፣ ትምህርታዊ እና የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ሴክተሮች ላይ ነው። መታሰቢያ በድርጅቷ በኩል ባህላዊ ቅርሶችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ኢኒሼቲቮችን ከጉግል አርትስ እና ካልቸር፣ ከኦሮሚያ ቱሪዝም እና ሌሎች የባህል ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መርታለች በተጨማሪም የልማት ኤጀንሲዎችን፣ የፊንቴክ ኩባንያዎችን እና የባህል ተቋማትን በአፍሪካ ኢኮኖሚ ውስጥ ስለገበያ መስፋፋትና ዲጂታላይዜሽን የማማከር አገልግሎት ሰጥታለች።[6]

የሚዲያ እና ዲጂታል መድረኮች

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መታሰቢያ እ.ኤ.አ በ 2022 ዓ.ም በወጣቶች ላይ ያተኮረ እና ለኢትዮጵያውያንና ለአፍሪካውያን ታዳሚዎች እንዲሆን ታስቦ የተቀረፀ D!NK ቲቪ የተሰኘ ሚዲያን መስርታለች።[7] በሚዲያው የተላለፈው ላጤ: ፍቅርን ፍለጋ የተሰኘው በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የእውነተኛ የፍቅር ጓደኝነት ተከታታይ ትዕይንት በአንድ ክፍል ከ600,000 በላይ እይታዎችን ያገኘ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ በስርዓተ ፆታ እና የፍቅር ግንኙነት ላይ አነጋጋሪ ለመሆን በቅቷል። ፕሮግራሙም ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ለማግኘት የበቃ ሲሆን እንደ ቢቢሲ እና ኦኬ አፍሪካ ባሉት የሚዲያ ተቋማት ሽፋንን አግኝቷል።[8][9]

ህትመቶች እና የሚዲያ አስተዋጽዖዎች

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መታሰቢያ ኤ ካልቸር ኦፍ ኮፊ የተሰኘ የቡና ባህል እና ታሪክን የሚዳስስ መጽሐፍ እ.ኤ.አ በ2013 ዓ.ም ለንባብ አብቅታለች[10][11][2]፤ መፅሀፉም በኮንግረስ ቤተ-መፃህፍት አርካይቭ ተደርጎ ይገኛል። እ.ኤ.አ. በ 2022 ዓ.ም በብሎክቼይን ላይ የተመሠረተ አመታዊ የስራውን እትም የማሻሻል ስራ፣ የWeb3 መተግበሪያዎችን ለባህላዊ ጥበቃ እና ለፈጣሪ የኢኮኖሚ ሞዴሎች የማሰስ ተግባርን መስርታለች። የእሷ ጽሑፍ እና አስተያየት በዘ ጋርዲያን [12]፣ ኳርትዝ አፍሪካ ፣ ናታል ሚዲያ[13][14] ፣ ሰላምታ መፅሄት[15] እና ሌሎች አለም አቀፍ ማሰራጫዎች ላይ ቀርበዋል። መታሰቢያ በቢቢሲ ኒውስ፣ ኦኬ አፍሪካ፣ እና ሌሎች የሚዲያ አውታሮች በባህል ፈጠራ እና በዲጂታል ሚዲያ ላይ ላበረከተችው አስተዋጽኦ ሽፋን አግኝታለች።.[7][9]

መታሰቢያ ለዲጂታል ሚዲያ፣ ለባህል ፈጠራ እና ለስነምህዳር ግንባታ ላበረከተችው አስተዋጾ እውቅናን ያገኘች ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ የሚከተሉት ተጠቃሾች ናቸው።

  • የኢንተርሌጀር ፋውንዴሽን ግራንት ፎር ዌብ ሽልማት፡ በዲጂታል ፋይናንስ እና Web3 ፈጠራ ላይ ላበረከተችው ፈር ቀዳጅ ስራ ሽልማትን አግኝታለች።[16]
  • የትሩ አፍሪካ ምርጥ 100 ፈጣሪዎች ሽልማት፡ እ.ኤ.አ. በ2015 በአፍሪካ የባህል እና ዲጂታል ዘርፎች ላይ ላደረችው አስተዋፅዖ እውቅናን አግኝታለች።[17]
  1. 1 2 "Design Week Addis Ababa wants to turn Ethiopia's growing economy into a creative one" (20 February 2019).
  2. 1 2 "Metasebia Yoseph's Transmedia Project: 'A Culture Of Coffee' at Tadias Magazine".
  3. Peck, Patrice (2015-09-02). "Metasebia Yoseph Wants To Make Addis Ababa A Global Design Capital | OkayAfrica" (በen-US).
  4. Tewodros, Rebecca (2022-12-03). "Design Week's Roaring Comeback" (በen-US).
  5. "Kifiya increases "Yene Guzo" service providers in Addis Ababa – New Business Ethiopia" (በen-US).
  6. Tewodros, Rebecca (2022-12-03). "Design Week's Roaring Comeback" (በen-US).
  7. 1 2 "Latey: Looking for Love - how Ethiopia's answer to The Bachelor sparked controversy" (በen-GB) (2025-04-20).
  8. "አስር ሴቶች፣ አንድ ወንድ፡ በኢትዮጵያ አነጋጋሪ የሆነው የመተጫጨት የቴሌቪዥን ሾው 'ላጤ'" (በam) (2025-04-21).
  9. 1 2 Adhis, Paula (2025-03-06). "'Latey: Looking for Love' is the Hit Ethiopian Reality Dating Show With an Unexpected Feminist Twist | OkayAfrica" (በen-US).
  10. "Writer pours her heart into sharing Ethiopians' coffee-drinking custom" (in en-US). The Washington Post. 2012-12-07. ISSN 0190-8286. https://www.washingtonpost.com/local/therootdc/2012/12/06/63476ba8-3e51-11e2-ae43-cf491b837f7b_story.html.
  11. Thomas, Langston (2022-05-17). "Monetizing IP in Web3: Building an Ecosystem Around Coffee and Literature" (በen-US).
  12. Yoseph, Metasebia (2015-06-29). "An insider's guide to Addis Ababa: Car crashes, coffee and contemporary art" (in en-GB). The Guardian. ISSN 0261-3077. https://www.theguardian.com/cities/2015/jun/29/insider-guide-addis-ababa-car-crashes-coffee-contemporary-art.
  13. "Ethiopia Skate".
  14. "Addis Art".
  15. "A Super Quick Guide to Addis Ababa". Ethiopian Airlines.
  16. "Metasebia Yoseph: The Founder of Design Week Addis Ababa" (2 November 2015).
  17. Metasebia Yoseph (14 December 2021). "Digital Gojo Grant Report #1 (Draft)".