Jump to content

ርትዕት ተዋሕዶ ሃይማኖት

ከውክፔዲያ

የርትዕት ተዋሕዶ ሃይማኖት

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የርትዕት ተዋሕዶ ሃይማኖት አስተምህሮ የቅድስት ሥላሴ አንድነት ሦስትነት የሚመለክ የሚሰገድለት ለአንድ አምላክ ለእግዚአብሔር ፈጣሪ፣ ምስጋና አምልኮ የሚገባውን አንድ እና አንድ እርሱ እንደ ሆነና፡ ምሥጢረ ሥላሴ አንድ አምላክ የሚታመን የመድኃኔዓለም ከሦስቱ ቅዱስ አንድ ቅዱስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወወልደ ድንግል ማርያም ሥግው የማዳን ምሥጢር ከሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ ተዋሕዶ የፈጸመልን ሰው ሁኖ ዓለምን ሁሉ ያዳነበት በተዋሕዶ ለሚያምን የእግዚአብሔር ውሉድ የሚሆን ሥልጣን የሰጠበት ትምህርተ አድኅኖ ወይ አስተምህሮ፡ የእግዚአብሔር ታላቅነት   ድንቅ ሥራ እና ተአምር የሚያስተምርበት የቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት መሆንዋን እናትነቷ ልመናዋ ቃል ኪዳንዋ እንዲሁም የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት የቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት ልመና እና ቃልኪዳናቸውን የሚያስረዳ የማያምን በእግዚአብሔር እንዲያምን ያመነም እንዲጸና በኃጢአት ያለም ንስሐ እንዲገባ በንስሐ እንዲመላለስ ሠላሳ ስልሳ መቶ ያማረ ፍሬ አፍርቶ መንግሥቱን እንዲወርስ የሚያስተምር ነው።

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የርትዕት ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ርቱዐን በመባል ይጠራሉ፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የበዓላት አከባበር

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በዐበይት በዓላት እና በሁለቱ ሰንበታት ገንዘብ መለዋወጥ መገበያየት ማዕድ ማሰናዳት እንጀራም ሆነ ዳቦ መጋገር የሚከተፉ ነገሮች ሁሉ አይፈቀዱም። የማዕድ መሰናዶ ለመጠጥ እና ለተለያየ አገልግሎት የሚውል ውኃ በየማጠራቀሚያው ማጠራቀም ከሐሙስ አንስቶ እስከ ዓርብ ሰባት ሰዓት መጠናቀቅ አለበት የዐበይት በዓላት ዋዜማ ላይ የቅድስት ሥላሴ የወላዲተ አምላክ የበዓለ ወልድ ዋዜማ ላይም በተመሳሳይ መልኩ ሰባት ሰዓት ላይ ባንቡኃ ይዘጋል ጠቅላላ ሥራ ያቆማል።

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ለዚህም ማስተማርያ ምሳሌ በነቢዩ ሙሴ ጊዜ ሕዝቡ የዕለተ ዓርብ እና የቀዳሚት ሰንበት መና በአንድ ላይ በዕለተ ዓርብ ወርዶ በዛው ዕለት ሰብስበው ያስቀመጡትን ነበር በቀዳሚት ሰንበት የተመገቡት አሁንም አስቀድሞ ማዕዱን በማሰናዳት በሰንበት በማሞቅ ብቻ መመገብ ይፈቀዳል።

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በሰንበታቱ እና በዐበይት በዓላት ይቅር በለን ከሚለው ሌላ ልመና አይፈቀድም። የምስጋና ቀናት ናቸውና በምስጋና፣ በዝማሬ፣ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማት፣ በመማማር፣ ስለ ቅዱስ ቃሉ በመነጋገር፣ የታመመን፣የታሰረን በመጠየቅ ምፅዋት በመመፅወት ለሥጋም በአግባቡ ዕረፍት በመውሰድ ይከበራል። መ.ኩፋሌ ፫(3)÷፲፱(19) "ከቀኑ ሁሉ ተለይታ ለበረከት እና ለቅድስና ለማመስገ(ኛ)ም ልትሆን ይህችን ቀን የፈጠረ የሁሉ ፈጣሪ ባረካት ይህ ሕግ ይህ ምስክር ለእስራኤል ልጆችና ለትውልዳቸውም ለዘለዓለም ሥርዓት ሆኖ ተሰጠ።"

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
የቡሔ አክባበር

ሥርዓተ ማዕድ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አንድ ክርስቲያን እርድ ሲያርድ የተያዘ ጾም ካለ ጾሙ ካለቀ በኋላ ከረቡዕ እና ዓርብ ከዐበይት በዓላት እና ከሁለቱ ሰንበታት ውጪ መሆን ይኖርበታል በሰንበት እርድ ስለማይፈቀድ ማለት ነው። እርድ በራሱ ሥራ ነውና በሰንበት ሥራ መሠራቱ ሰንበትን ያሽራል። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍትም በሰንበት ባርያህንም አሳርፈው እንስሳህንም ከተግባር ሥራ ሁሉ አሳርፈው ይላል፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ገድለ ተክለሐዋርያት ገጽ፳፫(23)-፳፮(26) "አባታችን ተክለሐዋርያት የቅዱሳንን ዐጽም በመጎብኘት በረከትን ይቀበሉ ዘንድ ቀን ወደ እንፍራዝ ሀገር ሄዱ። ዓርብ ማታ በሰንበት ዋዜማ ከአንድ ሰው ቤት ገብተው ያድሩ ዘንድ ወደ መንደር ገብተው እንዳስለመዱት በጸሎት ላይ ሳሉ አንዱን ዶሮ አርደው ይበሉት ዘንድ በከበቡት ጊዜ ከጌቶቹ አምልጦ እየሮጠ አባታችን ወዳሉበት ቦታ መጣ አባታችንም ዶሮውን ምን ሆንክ ብለው ጠየቁት ያን ጊዜ ዶሮው አንደበቱን ከፍቶ እንደ ሰው ለአባታችን ተክለሐዋርያት ተናገረ። አባታችንም ሰምተው አደነቁና አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ሥራህ ድንቅ ነው ምክርህም ጥልቅ ነው የማይናገረውን እንዲናገር ታደርጋለህ የሚናገረውን የሰው ልጅ ካልፈለክ ዲዳ ታደርጋለህ አሉ። ከጌቶቹ በሸሸ ጊዜ አውራ ዶሮው ለአባታችን ተክለሐዋርያት ነገራቸው። ያድኑትም ዘንድ ተማጸናቸው አባታችንም የዶሮውን ባለቤት ጠርተው ፈገግ በማለት ቀስ ብለው በየዋህነት በዚህ ዶሮ ላይ ምን አዘዝክ ወደ እኔ መጥቶአልና እነሆ ታየው ዘንድ በዚህ አለ አሉት። ነገር ግን አባታችን ዶሮ በሰው አንደበት የተናገረውን ለዚያ ሰው አልነገሩትም ደበቁት እንጂ። ይህ ነገር ለሥጋውያን ሰዎች የተሸሸገ ነውና። የዶሮውም ባለቤት ዛሬ አርደው ለምሳዬ በሰንበት ያዘጋጁልኝ ዘንድ አዝዤ ነበር ብሎ ለአባታችን ነገራቸው። አባታችንም ያንን ሰውየ ለእኔ ብለህ ሰንበት ስለሆነ ማርልኝ አትረደው ሰንበት ለፍጥረት ሁሉ ዕረፍት ናት። ለሰውም ለእንስሳትም ለአራዊትም ቢሆን ሰንበት ደስታ ናትና እንዳይጠምዷቸው እንስሳትን ያሳርፏቸው ዘንድ እንዲህ ብለው አባቶቻችን ሐዋርያት አዘዋልና አሉት። ነገር ግን አባታችን ስለ ሰንበት ክብር ያንን ዶሮ እንደያርደው በመከሩት ጊዜ ያ ሰው እሺ የማይል ሆነ። ይልቁንም ዶሮውን አርዶ ይበላው ዘንድ ወሰነ። አባታችንም ሰውየው ዶሮውን እንደማይተወው ሲያውቁ እኔ ዋጋውን እሰጥሃለው አሉት። ሰውየውም በዚህ ተስማምቶ እሺ አላቸው የዶሮውንም ዋጋ ሁለት እጥፍ የሚሆን ልብስ ከአባታችን ተቀበለ አባታችንም ይህን ልብስ የሰጠሁህ ዛሬ አትረድ ስላልኩህ ብቻ አይደለም ዶሮውን ምን ጊዜም እንዳትነካው በእርሱ ላይ ቢለዋን እንዳታነሳ በፈቃደ እግዚአብሔር እስከሚሞትበት ጊዜ ድረስ ነው እንጂ። ሲሞትም አራዊት እና አእዋፍ እንዳይበሉት አትጣለው በመሬት ውስጥ ቆፍረህ ቅበረው ከራሱ የሚበልጥ ዋጋ ሁለት እጅ የሚሆን ሰጥቼሃለሁና በማለት ዳግመኛ እንዳያርደው በእግዚአብሔር ስም አማሉት። ከዚህም በኋላ አባታችን ዶሮውን የሚበላውን ይፈልግ ዘንድ "እግዚአብሔር አድኖኃልና ሂድ" አሉት ዶሮውም ቃላቸውን ሰምቶ ራሱን ዝቅ አድርጎ ከእግራቸው ስር ወድቆ ሰግዶ ሕይወቱን ስላገኘ እየተደሰተ ወጥቶ ሄደ።" በማለት በሰንበት ዕርድ እንደማይፈቀድ ያስረዳል።

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የርቱዐን የዘመን መቁጠርያ ዘመነ ሔኖክ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ሔኖክ አቈጣጠር በሱባኤ የተለካ በዓላት እና አጽዋማት የማይዛነፉበት ዐበይት በዓላት ጥንተ ዕለታቸውን ጠብቀው የሚጓዙ ሲሆኑ አንድ ዓመት ሦስት መቶ ስልሳ አራት ቀናት አለው፡፡ ይህንንም መ.ሔኖክ ፳፰(28)÷፲፩(11) "ዓመቱም በሦስት መቶ ስልሳ አራት ቀን ይጨረሳል ነገሩም እውነት ነው የተጻፈውም ቊጥሩ የተጠነቀቀ ነው።" በማለት ሲገልጥ መ.ኩፋሌ ፯(7)÷፴(30) ደግሞ "አንተም የእስራኤልን ልጆች በዓመቱ በዚህ ቁጥር ሦስት መቶ ስልሳ አራት ቀንን ይጠብቁ ዘንድ እዘዛቸው የተቈጠረ ዓመትም ይሁን።" ሲል ያስረዳል። በዘመነ ሔኖክ ቀዳሚው ወር መጋቢት ነው ስያሜውም መገበ ሾመ ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን በወራት ሁሉ ላይ የተሾመ ነው። ስለዚህ ወር መ.አስቴር ፰(8)÷፱(9) "በዚያን ጊዜም ኒሳን በተባለው በመጀመሪያው ወር ከወሩም በሀያ ሦስተኛው ቀን የንጉሡ ጸሐፊዎች ተጠሩ.." በማለት ሲነግረን ድርሳነ ራጉኤል ዘሚያዝያ ክፍል ሁለት ቊጥር ሁለት እንዲህ ይላል በሁለተኛው ወር ማለት በሚያዝያ አንድ ቀን የመላእክት አለቃ ራጉኤል ዳግመኛ ወደ ንጉሡ ወደ ልብነ ድንግል መጥቶ ንጉሥ ልብነ ድንግል ሆይ የምነግርህን ስማ የማስረዳህንም ልብ አድርግ አስተውል አለው።" በማለት ሚያዝያ ሁለተኛ ወር መሆኑን መጋቢት አንደኛ ወር መሆኑን ይመሰክራል። ድርሳነ ጽዮን ዘሰኑይ ከምዕራፍ አንድ በፊት ቊጥር ሀያ ላይ "ሕዝቡ ከተሻገሩ በኋላ ታቦተ ጽዮንን የተሸከሙት ካህናት ወጡ። ዮርዳኖስም እንደ ቀድሞው እስካፋፉ ድረስ ሙሉ ሆነ ይኸን ያደረገችም ሰማያዊት ጽዮን ናት። ይኸውም ቀዳማይ ወርኅ በተባለው በሰብራልዮስ ወርኅ መጋቢት ፲ ቀን ነው።" ሲል ያረጋግጥልናል ማለት ነው።

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በዘመነ ሔኖክ ዓመቱ አራት ወቅታት ሲኖሩት እያንዳንዱ ወቅት በእሑድ ዕለት ተነስቶ በምልክቷ በዘጠና አንደኛዋ ቀን በዕለተ ቅዳሜ ያበቃል። የወቅቱ መግቢያ ቀናት ዕለተ እሑድ የሚውሉት ሰንበተ ሰንበታት ሲባሉ የወቅቱ መፈጸሚያ ቀናት የምልክት ቀን በመሆን ወቅትን ከሌላ የሚለዩት ዕለተ ቅዳሜ የሚውሉት የመለያ ወይም የምልክት ቀን ይባላሉ።

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በዓለ ትንሣኤ ሚያዝያ ፲፫(13) ሲሆን በዓለ ልደት ገና ደግሞ ታኅሣሥ ፲፯(17) ዕለተ ሠሉስ ይውላል ይህም በመ.ኩፋሌ ፬(4)÷፲፯(17) ላይ "ሁለተኛውም ወር በባተ በአሥራ ሰባተኛው ቀን በምድር ላይ የሚሄድ እባብ መጥቶ ወደ ሔዋን ቀረበ.." ብሎ ከዚያም ከገነት የወጡበት ቀን መሆኑን ያስቀምጣል። ዲያብሎስ በእባብ ተሠውሮ በአሥራ ሰባተኛው ቀን ከገነት እንዳወጣ(ቸ)ው መድኃኔ ዓለም አምላክነ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ እና ከነፍሷ ተዋሕዶ ሊያድናቸው በአሥራ ሰባተኛው ቀን ተወለደ። በመ.ኩፋሌ ፮(6)÷፳፱(29) "እግዚአብሔርም በአሥራ ሰባተኛው ቀን ማታ ጊዜ መርከቡን በውጪ ዘጋው እግዚአብሔር ሰባቱን የሰማይ ሻሻቴ ከፈተ ሰፊ የሆነ የጥልቁንም ውኃ በሰባ ስቁረት አወጣው።" በማለት እንደተገለጸው የጥፋት ውኃም በአሥራ ሰባተኛው ቀን ጀምሮ በመ.ኩፋሌ ፯(7)÷፩(1) ላይ"በአሥራ ሰባተኛው ቀን በሁለተኛው ወር ምድር ደረቀች።" የጥፋት ውኃ በዚሁ ቀን እንደደረቀ መድኅን እግዚእም በዚሁ ቀን ተወልዶ የዕዳ ደብዳቤ ደመሰሰልን አደረቀልን።

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የመድኃኔ ዓለም እና የቅድስት ድንግል ማርያም ማኅበር ዘ - ኢትዮጵያ አመሠራረት

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በቅድሚያ ማኅበሩ የተመሠረተው በንግሥተ ሰማይ ወምድር በወላዲተ አምላክ ፈቃድ እንደሆነ ማኅበሩ ያምናል፡፡ በመቀጠልም በንግሥተ ነገሥታት እኅተ ማርያም ዘ - ኢትዮጵያ አቢሲኒያ አሳሳቢነት ተመሠረተ፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ስለ ንግሥተ ነገሥታት እኅተ ማርያም ዘ - ኢትዮጵያ አቢሲኒያ በጥቂቱ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ንግሥተ ነገሥታት እኅተማርያም ዘ - ኢትዮጵያ አቢሲኒያ የመድኃኔ ዓለም እና የቅድስት ድንግል ማርያም ማኅበር ዘ - ኢትዮጵያ የበላይ ጠባቂ ሲሆኑ ማኅበሩንም ከወላዲተ አምላክ ትእዛዝ በመቀበል እየመሩ እንደሚገኙ ማኅበሩ ያምናል፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ግብርና

ርቱዐን የማይቀበሉት እውነታዎች

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
  • እየሱስ ክርስቶስ የሚለውን ስም አይቀበሉም በሱ ፈንታ በግእዙ መድኅን እግዚእ መድኃኔ ዓለም የሚለውን ነው የሚቀበሉት
  • መድኃኔ ዓለም በእስራኤል ሳይሆን በኢትዮጵያ መወለዱን እና መድኃኔ ዓለም በሥጋ ያከናወናቸው ተግባራት ሁሉ የተፈጸመው በኢትዮጵያ ውስጥ ብለው ያምናሉ
  • መድኃኔ ዓለም የተጠመቀው በዮርዳኖስ ሳይሆን በኢትዮጵያ በጊሆን ወንዝ ነው ብለው ያምናሉ
  • መድኃኔ ዓለም በምድር ላይ የኖረው 33 ዓመት ሳይሆን 42 ዓመት ነው ብለው ያምናሉ
  • ወላዲተ አምላክ እድሜዋ 64 ሳይሆን 72 ነው ብለው ያምናሉ
  • በመድኃኔ ዓለም ትንሣኤ ዕለት ቀድማ የተገኘች ወላዲተ አልምላክ ናት ብለው ያምናሉ
  • አሁን በኢትዮጵያ ላይ የሚተገበረውን የዘመን አቆጣጠር (ባህረ ሀሳብ) አይቀበሉም፣ የሚቆጥሩትም በዘመነ ሔኖክ ሲሆን ይህም አንድ አመት 364 ቀን ተብሎ በመፅሐፈ ሔኖክ እና በኩፋሌ እንደተቀመጠ ይጠቅሳሉ። አሁን በእነርሱ አቆጣጠር 2023 ዓም ነው (2017 በባህረ ሀሳብ አቆጣጠር እና 2025 እኤአ)
  • ካቴድራልን አይቀበሉም የተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ክብ ሆና ሦስት በር ያላት መሆኗን ያምናሉ
  • የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍላት 104 እንደሆኑ ያምናሉ፣ አሁን በአለም ላይ ያለው መፅሐፍ ቅዱስ የተቀነሰ መሆኑን ያምናሉ
  • ርቱዓን በቀን 7 ጊዜ ጸሎት ያደርሳሉ እነዚህም ጸሎታት አቡነ ዘበሰማያትን ጨምሮ በግእዝ ነው የሚያደሱት