ሀራሬ

ከውክፔዲያ
(ከሳልስበሪ ሮዴዚያ የተዛወረ)

ሀራሬ (Harare) የዚምባብዌ ዋና ከተማ ነው።

ሃራሬ

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢው ኗሪ ሲጨመር 2,800,111 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 1,600,000 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 17°50′ ደቡብ ኬክሮስ እና 31°03′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

1883 ዓ.ም. በእንግሊዝ ወታደሮች ተሠርቶ ምሽግ ሆኖ ስሙ 'ፎርት ሳሊስቡሪ' ተባለ። በ1889 ዓ.ም. በምሽጉ ዙሪያ ከተማ ስላደገ ስሙ ሳሊስቡሪ ሆነ። በ1974 ዓ.ም. ስሙ ሃራሬ ሆነ።