ሶሀባ (sahabah)/ኡሙ አይመን በረካ(ረ.ዐንሁ)

ከውክፔዲያ

Hayatu sohaba(ሶሀባ): ☞የኡሙ አይመን በረካ ታሪክ☜ ሱብሃን አሏህ !!! "ከእናቴ ቡኃላ እናቴ ነሽ" ረሱል (ሰ.ዐ.ወ)

❀በባሪያ ንግድ ወቅት ያች ወጣት ኢትዮዺያዊት ሴት በረካ እንዴት መካ ውስጥ ለሽያጭ እንደበቃች ባይታወቅም እንዲሁም የዘርሃረጓ፤ እናቷ ማን እንደሆነች ፣ አባቷ ማንእንደሆነ ወይም ቅድመአያቶቿ ማን እንደሆኑ ባይታወቅም እሷን መሰል ወጣት ወንዶችና ሴቶች አረቦችም ሆኑ አረብ ያልሆኑ ነገርግን ተይዘው ወደ ባሪያ ገበያ ለሽያጭ የበቁ በርካቶች ነበሩ። .." " ,,,, ❀በመጥፎ የባሪያ ገዥዎች እጅ የወደቀ ባሪያ መጥፎ እድል የሚገጥመው ሲሆን አብዛሃኛዎቹም ጉልበታቸውን ከልክ በላይ ይበዘብዟቸዋል ከልክ በላይ በሆነ ግፍና በደል ይይዟቸዋል ። በዚህ ሁኔታ ላይ እድለኞች የሆኑ እጅግ በጣም ጥቂቶች ናቸው። `` ``

❀ወጣት ኢትዮዺያዊት ሴት በረካ ከእድለኞቹ መካከል ስትሆን ደግና ቸር የነበረው የአብዱል ሙጦሊብ ልጅ አብዱሏህ የራሱ አደረጋት። በእርግጥም በቤቱ ውስጥ ብቸኛዋ አገልጋይ ሆነች። አብዱሏህ አሚናን ባገባ ጊዜ በረካ (ረ.ዐ) ሁሉንም ጉዳዮቿን የምትጠብቅ እና የምትቆጣጠር ሆነች።

`` እንደ በረካ ገለፃ ሁለቱ ጥንዶች ከተጋቡ ከሁለት ሳምንታት ብኋላ የአብዱሏህ አባት ወደ ቤታቸው መጣና ከነጋዴዎች ጋር ወደ ሶሪያ ለንግድ እንዲሄድ አዘዘው። አብዱሏህም ትዕዛዙን ተቀብሎ ሄደ። ❖ ❖ ❖ ❀ይህን ተከትሎ አሚና በጥልቅ አዘነች፤ አለቀሰችም። ምን ያልተለመደ ነገር ነው! ገና ሙሽሪት ሆኜ በእጄ ላይ ያለው ሂና ሳይለቅ እንዴት ባሌ ለንግድ ወደ ሶሪያ ይሄዳል? ስትል አሚና በጣም አዘነች። `` `` `` ❀የአብዱሏህ መነጠል ልብ የሚሰብር ነበር። እናታችን አሚና በጭንቀት ላይ ሆና ራሷን ሳተች። በረካም እንዲህ ትላለች አሚና እራሷን ስታ ሳያት በጭንቀት እመቤቴ ሆይ! ስል ጮኹኩኝ። አሚናም አይኖቿን ከፈት አድርጋ እያነባች ተመለከተችኝ። ማቃሰቷን አምቃ በረካ ወደ አልጋው ውሰጅኝ አለች። ይህን ተከትሎ አሚና ለረጅም ጊዜ የአልጋ ቁራኛ ሆነች። ማነንንም አታናግርም፤ ማንንም አትመለከትም ፤ ያሽማግሌ ታላቅ ሰው አብዱል ሙጦሊብ ሲቀር።

አብዱሏህ ተነጥሏት ከሄደ ከሁለት ወር ብኋላ አንድ ቀን ጧት ንጋት ላይ አሚና ጠራችኝ። ፊቷም በደስታ ይበራ ነበር። እንዲህ አለችኝ በረካ ሆይ! ያልተለመደ(እንግዳ) የሆነ ህልም አየሁ። እመቤቴ! ደስየሚል ነገር ነው? አልኴት። ብርሃን ከሆዴ ወጥቶ በመካ ዙርያ ያሉ ተራራዎችን ፣ ኮረብታዎችን እና ሸለቆዎችን ሲያበራ አየሁ። እመቤቴ! የነፍሰጡርነት ስሜት ይሰማሻል እንዴ? አልኴት። አዎ በረካ! ነገርግን ሌሎች ሴቶች እንደሚሰማቸው የምቾት ማጣት ስሜት እይሰማኝም አለች።

ሱብሃን አላህ መልካም ነገር ይዞ የሚመጣ የተባረከ ልጅ ትወልጃለሽ አልኴት። አብዱሏህ ከአሚና ከተለየበት ጊዜ አንስቶ በሐዘንና በትካዜ ላይ ወደቀች። በረካ(ረ.ዐ) ከጐኗ ሁና እያወራቻትና የተለያዩ ታሪኮችን እየተረከችላት ታፅናናት ነበር። " " አብርሃ ተብሎ የሚጠራ የየመን ገዥ ከተማውን እያጠቃ ስለነበር አብዱል ሙጦሊብ ቤቷን ትታ ወደ ተራራው እንድትሰደድ ሲነግራት የበለጠ አዘነች። አሚናም በጣም ሐዘን ላይ እንደሆነችና ወደ ተራራው ለመውጣት ደካማ እንደሆነች እንዲሁም አብርሃ ወደ መካ ገብቶ ካዕባን በፍፁም እንደማያጠፋውና በአሏህ የተጠበቀ እንደሆነ ስትነግረው በጣም ተበሳጨባት። ይሁን እንጂ ከአሚና ፊት የፍርሃት ምልክት አይታይም ነበር። በረካ እንዲህ ትላለች ቀንም ማታም ከጐኗ ነኝ። ሆኖም ከአልጋዋ ስር ስለነበር የምተኛው እያቃሰተች ባሏን ስትጠራ እሰማትታለሁ። ማቃሰቷ ይቀሰቅሰኝ ስለነበር ተነስቼ ላፅናናት እና ላጀግናት እሞክራለሁ። " " ከፊሎቹ ነጋዴዎች ከሶሪያ በተመለሱ ጊዜ ቤተሰቦቻቸው በእልልታ ተቀበሏቸው። በረካ ስለአብዱሏህ ሁኔታ ለማወቅ ወደ አብዱል ሙጦሊብ ቤት ተደብቃ በሚስጥር ሄደች። ነገርግን ስለእሱ ምንም ዜና አልነበረም። ወደ አሚና ተመልሳ ሄደች። ሆኖምግን እንዳታዝን እና እንዳትጨነቅ በማሰብ ያየቸችውንና የሰማችውን ነገር አልነገረቻትም። በመጨረሻም ሙሉ ነጋዴዎች ተመለሱ፤ አብዱሏህ ግን እነርሱ ጋር አልነበረም። ብኋላ ላይ የአብዱሏህ መሞት ዜና በመጣ ጊዜ በረካ ከአብዱል ሙጠሊብ ቤት ነበረች። እንዲህ ትላለች ዜናውን ስሰማ ጮኹኩኝ። ከዛ ብኋላ ምን እንደማረግ አላውቅም። እየጮኹኩ ወደ አሚና ቤት ሄድኩ። " ፡ " አብዱሏህ ተወዳጅ የነበረ፤ ለረጅም ጊዜ የጠበቀቅነው፤ መልከመልካም የመካ ወጣት፤ የቁረይሾች ኩራት ነበር። አሚና ይህን አሳማሚ ዜና ስትሰማ ራሷን ሳተች። እኔም በመኖርና በመሞት አፋፍ መካከል ሆና ያለ ከአልጋዋ ጐን ሆኜ አስታመምኴት። እኔ ብቻ ስቀር ከአሚና ቤት ማንም አልነበረም። እናም ልጇን እስክትወልድ ድረስ ቀኑንም ሌሊቱንም ከጐኗ ሆንኩ። " " ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) በተወለዱ ጊዜ በእጆቿ እቅፍ ያደረገቻቸው የመጀመሪያዋ በረካ ነበረች ። ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ ገላጣው በረሃ ሐሊማ ጋር በተላኩ ጊዜ በረካ ከአሚና ጋር ቆየች። ከ5 ዓመት ብኋላ ወደ መካ መጡ፤ አሚናም በፍቅር በደስታ ተቀበለቻቸው። ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ስድስት ዓመት ሲሞላቸው እናታቸው አሚና በያስሪብ የሚገኘውን የባሏን መቃወብር ልትጐበኝ ወሰንች። በረካ እና አብዱል ሙጠሊብ ሊያግባቧት ቢሞክሩም አሚና ቆርጣ ስለተነሳች አልተቀበለቻቸውም። እናም አንድ ቀን ጧት ጉዞ ጀመሩ። ይሁእንጂ ልጇን ከሃዘን እና ከጭንቀት ለማዳን አሚና ለሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የአባታቸውን መቃብር ልትጐበኝ እየሄደች መሆኑን አልነገረቻቸውም።

`` አብዛሃኛውን ጊዜም ነብያችን ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ከበረካ አንገት አካባቢ እጃቸውን ተደግፈው ይተኙ ነበር። አሚና የአብዱሏህን መቃብር በጐበኘባቸው ጊዜ ውስጥ የበለጠ በሃዘን ተጐሳቆለች። ወደ መካ እየተመለስን እያለ አሚና ባሳሳቢ ሁኔታ ታመመች። `` `` በያስሪብ እና በመካ መከካል አል-አብዋ ተብሎ በሚጠራ ቦታ የአሚና የጤንነት ሁኔታ በፍጥነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደረሰ። አንድ ቀን ምሽት ሰውነቷ ግሎ በሚተናንነቅ ድምፅ በረካ! በረካ! ስትል ጠራችኝ። በረካ እንዲህ ስትል ትተርካለች:- በረካ ሆይ! በቅርቡ ይህን አለም እነጠላለሁ፤ ልጄን ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ተንከባከቢው፤ በሆዴ ውስጥ ሆኖ ያለ አባቱን አጣ አሁን ደግሞ እናቱን ሊያጣ ነው። አንች እናት ሁኝው፤ አትተይውም ስትል በጆሮየ ሹክ አለችኝ። ልቤ ተንቀጠቀጠ እናም ማልቀስ ጀመርኩ። በእኔ ለቅሶ ህፃኑም ማልቀስ ጀመረ። እራሱን ወደ እናቱ እጆች ወረወረና በአንገቷ ጥምጥም አለ። እንዴ አቃስታ አሸለበች።


በረካ አምራ አለቀሰች። በእጆቿ ከአሸዋው መቃብሯን ቆፍራ ቀበረቻት። ከልቧ በቀረው እንባዋ መቃብሯን አራሰችው። በረካ ከሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መካ ተመልሳ በአያታቸው እንክብካቤ ስር እንዲሆን አደረገች። ልጁን ለመንከባከብ እና ለመጠበቅ ከቤቱ ሆና የቆየች ሲሆን አብዱል ሙጦሊብ ከሁለት ወር ብኋላ ሲሞት ልጁን ይዛ ወደ አጐቱ አቡጧሊብ ሄደች። እናም ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እስኪያድጉና ኸድጃ(ረ.ዐ) እስኪያገቡ ድረስ ተንከባክባ ፣ ፍላጐታቸውን አሟልታ አሳደገቻቸው።

` በረካ ከሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ከኸድጃ ቤት መኖር ጀመረች። በፍፁም ትቼው አላውቅም እሱም በፍፁም ትቶኝ አያውቅም ትላለች። አንድ ቀን ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ጠሩኝና እናቴ ሆይ! አሁን አግብቻለሁ አንቺ ደግሞ እስካሁን አላገባሽም የሆነ ሰው ቢመጣና ለጋብቻ ቢጠይቅሽ ምንታስቢያለሽ? አሉኝ። በረካም

ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) እየተመለከተች በፍፁም ትቼህ አልሄድም። እናት ልጇን ትተዋለች እንዴ? አለች። ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ አሉና ግንባሯን ሳምምምም! አደረጓት።

ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ሚስታቸውን ኸድጃ(ረ.ዐ) እየተመለከቱ ይች በረካ ከእናቴ ቀጥሎ እናቴ ናት። ቀሪ ቤተሰቤ እሷናት አሉ። ኸድጇ (ረ.ዐ) በረካን እየተመለከተች በረካ ሆይ! ለሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ስትይ ወጣትነትሽን መስዋዕት አደረግሽ አሁን ደግሞ እሱ ሊክስሽ ይወዳል። ለሱም ለኔም ስትይ እርጅና ሳይጫጫንሽ አግቢ ትላታለች። በረካም ማንነው የማገባው እመቤቴ? ስትል ትጠይቃታለች። ከኸዝረጅ ጐሳ የሆነ ኡበይድ ኢብን ዘይድ ለጋብቻ ፈልጐሽ ወደኛ መቶ ነበር። ለእኔስትይ እምቢ አትበይኝ? በረካ ተስማምታ ኡበይድ ኢብን ዘይድን አገባች። ከእርሱም ጋር ወደ ያስሪብ ሄዳ እዚያው ልጅ ወለደች፤ ልጇንም አይመን ስትል ጠራችው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኡሙ አይመን (የአይመን እናት) እየተባለች ትጠራለች። ባሏ ሲሞትባት ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ለመኖር ወደ መካ ሄደች። ከኸድጃ ቤት በረካን ጨምሮ አሊ ኢብን አቢጧሊብ እና ዘይድ ኢብን ሐሪሳ ነበሩ።

አንድ ቀን ምሽት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ዘወትር ሶኻባዎቻቸውን ሰብስበው ወደ ሚያስተምሩበት የሚወስደውን ምንገድ ሙሽሪኮች ዘጉት። በዚህ ወቅት ኸድጃ ለረሱል (ሰ.ዐ.ወ) አስቸኴይ መልዕክት ስለነበራት በረካ ሂወቷን መስዋዕት አድርጋ ከተሰባሰቡበት ቦታ ለመድረስ ሞከረች። በደረሰች ጊዜ መልዕክቱን ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አደረሰች። ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ አሉና እንዲህ አሏት:- የአይመን እናት ሆይ! አንች የተባረክሽ ነሽ በእርግጥም ``በጀነት`` ቦታ አለሽ አሏት።

❖❖ ኡሙ አይመን በሄደች ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሱኻባዎቹን ተመለከቱና ከጀነት የሆነችን ሴት ከእናንተ መካከል ማግባት የሚሻ አለን? . ኡሙ አይመንን ያግባ አሉ። ሁሉም ሱኻባዎች ፀጥ አሉ። አንዲትን ቃል እንኴ ትንፍሽ አላሉም።

በጊዜው ኡሙ አይመን ወጣት ያልነበረች ሲሆን ውበቷ ጠውልጓል። በዚህ ወቅት 50 ዓመቷ ነበር። ነገር ግን ዘይድ ኢብን አልሐሪሳ ወደ ፊት መጣ አለና የአሏህ መልዕክተኛ ሆይ! እኔ ኡሙ አይመንን አገባታለሁ። በአሏህ ይሁንብኝ! ግርማሞገስና ውበት ካላት ሴት በላጭ ናት አለ። ዘይድና ኡሙ-አይመን ተጋብተው ልጅ ወለዱ፤ ልጃቸውንም ኡሳማ አሉት። ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) እንደ ልጃቸው ይወዱታል። ኡሳማ በወጣትነት ጊዜው እራሱን ለኢስላም ማገልገል ጀመረ። ብኋላ ላይ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ከባድ ሃላፊነት ሰጡት። ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ወደ መዲና ሲሰደዱ ኡሙ-አይመን ቤታቸውን እንድትቆጣጠርላቸው እዛው መካ ትተዋት ሄዱ። በመጨረሻ ላይ ግን በራሷ ወደ መዲና ተሰደደች። በዛ በረሃማና ተራራማ መሬት ረጅም እና አስቸጋሪ የሆነ ጉዞ በእግሯ ተጓዘች። ሙቀቱ በጣም የሚያቃጥል ሲሆን አሸዋ ይዞ የሚነፍሰው ንፋስ መንገዱን ይጋርድባት ነበር። ነገርግን ለሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ከነበራት ጥልቅ ፍቅር ምክኒያት ፀጥንታ ጉዞዋን ቀጠለች። መዲና ስትደርስ እግሮቿ አብጠውና ቆስለው፤ ፊቷ በአሸዋና በአፈር ተሸፍኖ ነበር። ኡሙ-አይመን ሆይ! እናቴ ሆይ! በእርግጥም በጀነት ቦታ አለሽ አሏት። አይኖቿንና ፊቷን ጠረጉላት፤ እግሮቿን እና ትካሻዋንም አሻሿት። `` በረካ በተለያዩ ዘመቻዎችና ጦርነቶች ተሳትፋለች። ለምሳሌ:- በኡኹድ ውሃ ለተጠሙት ውሃ ታከፋፍላለች፤ የቆሰሉትንም ትጠብቃለች። በኸይበር እና በኹነይን ዘመቻ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) አጅባለች። ልጇ አይመን የተገደለው በኹነይን ዘመቻ ነበር።

ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ከሞቱ ቡኋላ ከበረካ አይኖች እንባ አይጠፋም ነበር። አንዴ ለምንድ ነው የምታለቅሽው ተብላ ተጠይቃ በአሏህ ይሁንብኝ የአሏህ መልዕክተኛ እንደሚሞቱ አውቃለሁ ነገርግን የማለቅሰው ወህዩ ስለተቇረጠብን ነው ስትል መለሰች።

በረካ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ከተወለዱበት ጊዜ አንስቶ እስከሞቱበት ጊዜ ድረስ ከጐናቸው ነበረች። ለእስልምና ሃይማኖት የነበራት ፍቅር እጅግ በጣም ጠንካራ ሲሆን የሞተችው በኸሊፋው ኡስማን ዘመን ነበር። ረዲየሏሁ አንሃ