ቀላዋ

ከውክፔዲያ
ቀላዋ

ቀላዋ (Maesa lanceolata) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ትልቅ ቊጥቋጦ እስከ 7 ሜትር ይደርሳል። ታላላቅ ቅጠልና ቀይ-ቡናማ ልጥ አለው። ቅጠሉ ቢሰበር ቡናማ ሙጫ ይወጣል።

አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በደጋ ጫካዎች ተራ ነው። በፈሳሽ ዳርና በጫካ ዳር ይገኛል። በአፍሪካ፣ ደቡብ አረቢያና ማዳጋስካር ይገኛል።

የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቢጫ ክብ ፍሬዎች ዘይት ይሰጣል፣ ይህም ዘይት አዲስ ሸክላ ለመደፈን ትልንም ለመግደል ይጠቀማል።

የቅጠሉ ውጥ ለአሣ መርዝ ነው፤ ዛጎል ለበስንም ይገድላል።[1]

የኮሶ ትልን ለማስወጣት፣ የቀላዋ ሥር ተደቅቆ በውሃ ይጠጣል።

እባብ ነከስ፣ የቀለዋ ቅጠል ይኘካል።[2]


  1. ^ አማረ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  2. ^ በደብረ ሊባኖስ ዙሪያ ያለው ሕዝብ መድሃኒታዊ እጾች እውቀናና ጥቅም 1998 ዓም ከጥላሁን ተክለሃይማኖት፣ ሚሩጸ ጊዳይ፣ ግርማይ መድኅን፣ ያለም መኮነን፣ አዲስ አበባ ዩኒቬርሲቴ፣ አክሊሉ ለማ ተቋም