ቃለ ዐዋዲ
የቅድስት ቤተ ክርስትያንን አንድነትና አስተዳደር ለማጠናከር ለአራተኛ ጊዜ ተሻሽሎ የወጣ[1]
የስበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ደንብ
- ↑ የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርዝትያን ሲኖዶስ፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተዘጋጀውን ቃለ ዓዋዲ ምርህ።
ቃለ ዓዋዲ የተባለው መጽሐፍ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ያለውን አስተዳደራዊ መዋቅር ያካተተ የሕግ መጽሐፍ ነው፡፡ በዚህም ብቻ ሳይወሰን ከምእመናን ጀምሮ እስከ ካህናት ድረስ ያሉትን የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች መብትና ግዴታ በውሉ የሚያስገነዝብ መመሪያም ነው፡፡[1]
- ↑ በእኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ስንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ
ሕገ ቤተ ክርስቲያን
ጠቅላላ ድንጋጌዎች እና መሠረታዊ መርሖች ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ
፩ አጭር ርእስ
ይህ ሕግ ‘‘የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ቤተ ክርስቲያን ቁጥር ፩/፳፻፲፭” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡[1]
አንቀጽ ፪ ትርጓሜ
፩. ‘‘ቤተ ክርስቲያን” ማለት ክርስቶስን በተዋሕዶ አንድ አካል፣ አንድ ባሕርይ ብላ የምታምን ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲት፣ ታሪካዊት፣ ኲላዊት፣ሉዓላዊት፣ ብሔራዊት እና ዓለማቀፋዊት ቅድስት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማለት ነው፡፡
፪. ‘‘ቅዱስ ሲኖዶስ” ማለት ቅዱስ ፓትርያርክ፣ ሊቃነ ጳጳሳት፤ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት የሚገኙበት ዐቢይ ጉባኤ ሆኖ ከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ሕግ አውጪና ወሳኝ አካል ነው፡፡[2]
፫. ‘‘የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ” ማለት በዓመት ሁለት ጊዜ የሚሰበሰብና መላው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሚገኙበት ጉባኤ ነው፡፡
፬. ‘‘ፓትርያርክ” ማለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርእሰ አበው፣ አበ ብዙኃን እና መሪ ማለት ነው፡፡
፭. ‘‘ቋሚ ሲኖዶስ” ማለት ቅዱስ ፓትርያርክ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፣ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት መካከል አራት ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ጳጳሳት ወይም ኤጲስ ቆጶሳት በአባልነት የሚገኙበት ጉባኤ ነው፡፡
፮.‘‘የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት” የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እና ቋሚ ሲኖዶስ መነጋገሪያ አጀንዳዎችን አዘጋጅቶ የሚያቀርብ፣ የሚወሰኑ ውሳኔዎችን ለሚመለከተው አካል የሚያስተላልፍና አፈጻጸሙን የሚከታተል ጽ/ቤት ነው፡፡
፯. ‘‘የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ” ማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጦ የተሠየመ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ዋና የሥራ መሪ ሊቀ ጳጳስ ነው፡፡
፰. ‘‘ሊቀ ጳጳስ” ማለት በኤጲስ ቆጶስነት (በጳጳስነት) ሲያገለግል ከቆየ በኋላ በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ በቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ በሊቀ ጳጳስነት መዓርግ የሚሠየም የቤተ ክርስቲያን አባት እና መሪ ነው፡፡
፱. ‘‘ኤጲስ ቆጶስ” ወይም ‘‘ጳጳስ” ማለት በድንግልና መንኲሶ ቤተ ክርስቲያንን በክህነት ሲያገለግል ቆይቶ የኤጲስ ቆጶስነትን መዓርግ የተቀበለ የቤተ ክርስቲያን ኖላዊ ወይም ጠባቂ ማለት ነው፡፡
፲. “መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት” ማለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ነው፡፡
፲፩. “ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ” ማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጦ የተሠየመ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና የሥራ መሪ ሊቀ ጳጳስ ነው፡፡
፲፪. “ምክትል ሥራ አስኪያጅ” ማለት ክህነት ያለው ሆኖ በጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቅራቢነት በቋሚ ሲኖዶስ ተመርጦ የተሠየመ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ነው፣
፲፫. “አስተዳደር” ማለት በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ያለውንና የድርጅቶችን አስተዳደርና አመራር የሚያጠቃልል የአስተዳደር ሥራ ነው፡፡
፲፬. “የአስተዳደር ጉባኤ” ማለት በጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ የሚመራ የመምሪያ ሐላፊዎች የሚገኙበት ስብሰባ ነው፡፡
፲፭. “መምሪያ” ማለት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሚገኝ ዐቢይ የሥራ ዘርፍ ነው፤
፲፮. “መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት” ማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተለይቶ የተከለለና በሊቀ ጳጳስ ወይም በኤጲስ ቆጶስ የሚመራ የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ክልል ነው፡፡
፲፯. “ድርጅት” ማለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የተቋቋመና የሚቋቋም ድርጅት ነው፡፡
፲፰. “ሥራ አስኪያጅ” ማለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመሥሪያ ቤቶችና የድርጅቶች ሥራ መሪ ነው፣
፲፱. “ሠራተኛ” ማለት በቤተ ክርስቲያኒቱ መሥሪያ ቤቶች በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ተመድቦ መንፈሳዊ፣ አስተዳደራዊ ወይም ሌላ ዓይነት አገልግሎት የሚያበረክት ሰው ነው፡፡
፳. “አገልጋይ” ማለት በማሕሌት ወይም በሌላ መንፈሳዊ ግልጋሎት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ተመድቦ በክፍያ ወይም በትሩፋት መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሰጥ ማንኛውም ሰው ማለት ነው፣
፳፩. “ቄስ” ማለት በሊቀ ጳጳስ /በኤጲስ ቆጶስ/ አንብሮተ እድ (እጅ በመጫን) በንፍኀት መንፈሳዊ ሥልጣን የተሰጠውና በቤተ መቅደስ በቅዳሴ፤ በውዳሴ፤ በዝማሬና በሰዓታት ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግል ኖላዊ /የምእመናን ጠባቂ / ባራኪ፤ ቀዳሽና ናዛዥ የንስሓ አባት ማለት ነው፡፡
፳፪ “ዲያቆን” ማለት በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት በሊቀ ጳጳስ /በኤጲስ ቆጶስ/ አንብሮተ እድ (እጅ በመጫን) የተሠየመ ላእከ ካህን ነው፡፡
፳፫ “ምእመን” ማለት በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት ተጠምቆ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባል የሆነ አማኝ ማለት ነው፡፡
፳፬ “መነኲሴ” ማለት በራሱ ፈቃድ ዓለማዊ ግብርን ሁሉ መንኖ(ትቶ) እንደ ሞተ ሰው ተገንዞ ጸሎተ ፍትሐት የተደረሰለት፤ የተጸለየበትና የተባረከን ቆብ የጫነ ካህን ወይም ምእመን ማለት ነው፡፡
፳፭ “ገዳም” ማለት የመነኰሳት ወይም የመነኰሳይያት በዓት (መኖሪያ) የሆነ ከዓለማዊ መንደር የራቀ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡
፳፮.“ደብር” ማለት የተሟላ አገልግሎት የሚፈጽምበትና በቅዱስ ፓትርያርክ ወይም በሊቀ ጳጳስ ደብር የሚል መዓርግ የተሰጠው ቤተ ክርስቲያን ነው ፡፡
፳፯. “ገጠር ቤተ ክርስቲያን” ማለት ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን በተሟላ ሁኔታ የሚሰጡበት ሆኖ ደብር የሚል መዓርግ ያልተሰጠው ቤተ ክርስቲያን ነው ፡፡
፳፰. “አበ ምኔት” ማለት የወንዶች ገዳም አስተዳዳሪ ወይም አባት ማለት ነው፡፡ ፳፱. “እመ ምኔት” ማለት የሴቶች ገዳም አስተዳዳሪ ወይም እናት ማለት ነው፡፡
፴. “አስተዳዳሪ” ማለት፤
ሀ. የገዳም መምህር (አበ ምኔት/እመ ምኔት)፣
ለ. የደብር አለቃ፤
ሐ. ለገጠር ቤተ ክርስቲያን ዋና ሐላፊ ሆኖ የተሠየመ ቄሰ ገበዝ ወይም ክህነት ያለው መሪጌታ ማለት ነው፡፡