Jump to content

ቃለ ዐዋዲ

ከውክፔዲያ

የቅድስት ቤተ ክርስትያንን አንድነትና አስተዳደር ለማጠናከር ለአራተኛ ጊዜ ተሻሽሎ የወጣ[1]

የስበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ደንብ

  1. የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርዝትያን ሲኖዶስ፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተዘጋጀውን ቃለ ዓዋዲ ምርህ።

ቃለ ዓዋዲ የተባለው መጽሐፍ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ያለውን አስተዳደራዊ መዋቅር ያካተተ የሕግ መጽሐፍ ነው፡፡ በዚህም ብቻ ሳይወሰን ከምእመናን ጀምሮ እስከ ካህናት ድረስ ያሉትን የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች መብትና ግዴታ በውሉ የሚያስገነዝብ መመሪያም ነው፡፡[1]

  1. በእኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ስንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ

ሕገ ቤተ ክርስቲያን

ጠቅላላ ድንጋጌዎች እና መሠረታዊ መርሖች ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ

፩ አጭር ርእስ

ይህ ሕግ ‘‘የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ቤተ ክርስቲያን ቁጥር ፩/፳፻፲፭” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡[1]

አንቀጽ ፪ ትርጓሜ

፩. ‘‘ቤተ ክርስቲያን” ማለት ክርስቶስን በተዋሕዶ አንድ አካል፣ አንድ ባሕርይ ብላ የምታምን ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲት፣ ታሪካዊት፣ ኲላዊት፣ሉዓላዊት፣ ብሔራዊት እና ዓለማቀፋዊት ቅድስት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማለት ነው፡፡

፪. ‘‘ቅዱስ ሲኖዶስ” ማለት ቅዱስ ፓትርያርክ፣ ሊቃነ ጳጳሳት፤ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት የሚገኙበት ዐቢይ ጉባኤ ሆኖ ከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ሕግ አውጪና ወሳኝ አካል ነው፡፡[2]

፫. ‘‘የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ” ማለት በዓመት ሁለት ጊዜ የሚሰበሰብና መላው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሚገኙበት ጉባኤ ነው፡፡

፬. ‘‘ፓትርያርክ” ማለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርእሰ አበው፣ አበ ብዙኃን እና መሪ ማለት ነው፡፡

፭. ‘‘ቋሚ ሲኖዶስ” ማለት ቅዱስ ፓትርያርክ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፣ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት መካከል አራት ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ጳጳሳት ወይም ኤጲስ ቆጶሳት በአባልነት የሚገኙበት ጉባኤ ነው፡፡

፮.‘‘የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት” የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እና ቋሚ ሲኖዶስ መነጋገሪያ አጀንዳዎችን አዘጋጅቶ የሚያቀርብ፣ የሚወሰኑ ውሳኔዎችን ለሚመለከተው አካል የሚያስተላልፍና አፈጻጸሙን የሚከታተል ጽ/ቤት ነው፡፡

፯. ‘‘የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ” ማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጦ የተሠየመ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ዋና የሥራ መሪ ሊቀ ጳጳስ ነው፡፡

፰. ‘‘ሊቀ ጳጳስ” ማለት በኤጲስ ቆጶስነት (በጳጳስነት) ሲያገለግል ከቆየ በኋላ በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ በቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ በሊቀ ጳጳስነት መዓርግ የሚሠየም የቤተ ክርስቲያን አባት እና መሪ ነው፡፡

፱. ‘‘ኤጲስ ቆጶስ” ወይም ‘‘ጳጳስ” ማለት በድንግልና መንኲሶ ቤተ ክርስቲያንን በክህነት ሲያገለግል ቆይቶ የኤጲስ ቆጶስነትን መዓርግ የተቀበለ የቤተ ክርስቲያን ኖላዊ ወይም ጠባቂ ማለት ነው፡፡

፲. “መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት” ማለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ነው፡፡

፲፩. “ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ” ማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጦ የተሠየመ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና የሥራ መሪ ሊቀ ጳጳስ ነው፡፡

፲፪. “ምክትል ሥራ አስኪያጅ” ማለት ክህነት ያለው ሆኖ በጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቅራቢነት በቋሚ ሲኖዶስ ተመርጦ የተሠየመ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ነው፣

፲፫. “አስተዳደር” ማለት በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ያለውንና የድርጅቶችን አስተዳደርና አመራር የሚያጠቃልል የአስተዳደር ሥራ ነው፡፡

፲፬. “የአስተዳደር ጉባኤ” ማለት በጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ የሚመራ የመምሪያ ሐላፊዎች የሚገኙበት ስብሰባ ነው፡፡

፲፭. “መምሪያ” ማለት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት የሚገኝ ዐቢይ የሥራ ዘርፍ ነው፤

፲፮. “መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት” ማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተለይቶ የተከለለና በሊቀ ጳጳስ ወይም በኤጲስ ቆጶስ የሚመራ የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ክልል ነው፡፡

፲፯. “ድርጅት” ማለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የተቋቋመና የሚቋቋም ድርጅት ነው፡፡

፲፰. “ሥራ አስኪያጅ” ማለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመሥሪያ ቤቶችና የድርጅቶች ሥራ መሪ ነው፣

፲፱. “ሠራተኛ” ማለት በቤተ ክርስቲያኒቱ መሥሪያ ቤቶች በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ተመድቦ መንፈሳዊ፣ አስተዳደራዊ ወይም ሌላ ዓይነት አገልግሎት የሚያበረክት ሰው ነው፡፡

፳. “አገልጋይ” ማለት በማሕሌት ወይም በሌላ መንፈሳዊ ግልጋሎት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ተመድቦ በክፍያ ወይም በትሩፋት መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሰጥ ማንኛውም ሰው ማለት ነው፣

፳፩. “ቄስ” ማለት በሊቀ ጳጳስ /በኤጲስ ቆጶስ/ አንብሮተ እድ (እጅ በመጫን) በንፍኀት መንፈሳዊ ሥልጣን የተሰጠውና በቤተ መቅደስ በቅዳሴ፤ በውዳሴ፤ በዝማሬና በሰዓታት ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግል ኖላዊ /የምእመናን ጠባቂ / ባራኪ፤ ቀዳሽና ናዛዥ የንስሓ አባት ማለት ነው፡፡

፳፪ “ዲያቆን” ማለት በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት በሊቀ ጳጳስ /በኤጲስ ቆጶስ/ አንብሮተ እድ (እጅ በመጫን) የተሠየመ ላእከ ካህን ነው፡፡

፳፫ “ምእመን” ማለት በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት ተጠምቆ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባል የሆነ አማኝ ማለት ነው፡፡

፳፬ “መነኲሴ” ማለት በራሱ ፈቃድ ዓለማዊ ግብርን ሁሉ መንኖ(ትቶ) እንደ ሞተ ሰው ተገንዞ ጸሎተ ፍትሐት የተደረሰለት፤ የተጸለየበትና የተባረከን ቆብ የጫነ ካህን ወይም ምእመን ማለት ነው፡፡

፳፭ “ገዳም” ማለት የመነኰሳት ወይም የመነኰሳይያት በዓት (መኖሪያ) የሆነ ከዓለማዊ መንደር የራቀ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡

፳፮.“ደብር” ማለት የተሟላ አገልግሎት የሚፈጽምበትና በቅዱስ ፓትርያርክ ወይም በሊቀ ጳጳስ ደብር የሚል መዓርግ የተሰጠው ቤተ ክርስቲያን ነው ፡፡

፳፯. “ገጠር ቤተ ክርስቲያን” ማለት ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን በተሟላ ሁኔታ የሚሰጡበት ሆኖ ደብር የሚል መዓርግ ያልተሰጠው ቤተ ክርስቲያን ነው ፡፡

፳፰. “አበ ምኔት” ማለት የወንዶች ገዳም አስተዳዳሪ ወይም አባት ማለት ነው፡፡ ፳፱. “እመ ምኔት” ማለት የሴቶች ገዳም አስተዳዳሪ ወይም እናት ማለት ነው፡፡

፴. “አስተዳዳሪ” ማለት፤

ሀ. የገዳም መምህር (አበ ምኔት/እመ ምኔት)፣

ለ. የደብር አለቃ፤

ሐ. ለገጠር ቤተ ክርስቲያን ዋና ሐላፊ ሆኖ የተሠየመ ቄሰ ገበዝ ወይም ክህነት ያለው መሪጌታ ማለት ነው፡፡

  1. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ቤተ ክርስቲያን
  2. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ቤተ ክርስቲያን