ቡሽ ባርኔጣ

ከውክፔዲያ
የታይላንድ ቤተ መንግሥት ዘበኞች

ቡሽ ባርኔጣቡሽ ወይንም ከግንደ ብሌን የተሠራ ባርኔጣ ሲሆን በዓለም ዙሪያ በአንዳንድ ወታደራዊ ወግ ልብስ እንዲሁም በሕዝቡ መካከል የሚታይ ቄንጥ ነው። ከሕንድ ቡሽ (ሾላፒስ) የተሠሩት ባርኔጦች መጀመርያ በስፓኒሾችፊሊፒንስ በ1840 ዓም አካባቢ ሲሆን፣ በሙቀት ሀገራት በገሞጂ በጣም ስለሚስማማ በቶሎ ወደ ፈረንሳይብሪታንያጣልያንጀርመን ኃያላት ተስፋፋ። በአንዳንዶች ዘንድ የቅኝ አገር ምልክት ቢታስብም፣ በተረፈ በበርካታ ሌሎች አገራት ተወዳጅነትና ሰፊ ጥቅም አግኝቷል። እስከ ዛሬ ድረስ በተለይ ለምሳሌ በቬትናምብሪታንያካናዳአሜሪካኔዘርላንድቶንጋ በአንዳንድ ጭፍሮች ሊታይ ይችላል፣ እንዲሁም የክብር ዘበኞች በታይላንድፊሊፒንስሞናኮዚምባብዌ እና ፖሊሶች ወይም የትራፊክ ፖሊሶች በስሪ ላንካሕንድጣልያን የቡሽ ባርኔጣን ለብሰውታል። በኢትዮጵያም በተለይ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት እስከ 1967 ዓም ድረስ በክቡር ዘበኞች እንዲሁም በጃንሆይ እራሳቸው ይታይ ነበር።

ቡሽ ባርኔጦች ብዙ ልዩ ልዩ ቅርጾች አሏቸው፣ በታይላንድ ዘበኞች በፎቶው እንደሚታይ አንዳንዴ አንድ ነጥብ በአናት ላይ አቁመዋል።