Jump to content

ቦምቤ

ከውክፔዲያ

ቦምቤ ( በወላይትኛ :Bombbe) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ዎላይታ የሚገኝ ከተማ ነው። [1] ቦምቤ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 325 ኪ.ሜ፣ ከዎላይታ ሶዶ ደግሞ በስተሰሜን ምዕራብ 55 ኪ.ሜ ላይ ይገኛል። [2] ቦምቤ ከተማ በወላይታ ዞን ቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ የአስተዳደር ዋና ከተማ ሆኖ ያገለግላል። ከተማው ከባህር ጠለል በላይ 5,023 ከፍታ ላይ ይገኛል። በከተማው ያሉት አገልግሎቶች የ24 ሰአት የኤሌክትሪክ መብራት፣ የንፁህ ውሃ አገልግሎት፣ አፀደ ህጻናት፣ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣቢያ፣ የእለት ተእለት የህዝብ ገበያ እና ሌሎችም ናቸው። ቦምቤ በ7°08'04"ሰሜን 37°34'54"ምስራቅ [3] መካከል ይገኛል።

የስነ ሕዝብ አወቃቀር

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቦምቤ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ህዝብ በብዛት የሚኖርበት ከተማ ነው። እ.ኤ.አ. በ2019 የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ባደረገው የህዝብ ትንበያ መሰረት የቦምቤ ከተማ በድምሩ 11,969 ህዝብ አላው ። ከዚህ አሃዝ ውስጥ ወንዶች 6,045 ሲሆኑ ሴቶች ደግሞ 5,924 ይሆናሉ። [4]