ቦምቤ
Appearance
ቦምቤ ( በወላይትኛ :Bombbe) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ዎላይታ የሚገኝ ከተማ ነው። [1] ቦምቤ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 325 ኪ.ሜ፣ ከዎላይታ ሶዶ ደግሞ በስተሰሜን ምዕራብ 55 ኪ.ሜ ላይ ይገኛል። [2] ቦምቤ ከተማ በወላይታ ዞን ቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ የአስተዳደር ዋና ከተማ ሆኖ ያገለግላል። ከተማው ከባህር ጠለል በላይ 5,023 ከፍታ ላይ ይገኛል። በከተማው ያሉት አገልግሎቶች የ24 ሰአት የኤሌክትሪክ መብራት፣ የንፁህ ውሃ አገልግሎት፣ አፀደ ህጻናት፣ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣቢያ፣ የእለት ተእለት የህዝብ ገበያ እና ሌሎችም ናቸው። ቦምቤ በ7°08'04"ሰሜን 37°34'54"ምስራቅ [3] መካከል ይገኛል።
ቦምቤ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ህዝብ በብዛት የሚኖርበት ከተማ ነው። እ.ኤ.አ. በ2019 የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ባደረገው የህዝብ ትንበያ መሰረት የቦምቤ ከተማ በድምሩ 11,969 ህዝብ አላው ። ከዚህ አሃዝ ውስጥ ወንዶች 6,045 ሲሆኑ ሴቶች ደግሞ 5,924 ይሆናሉ። [4]
- ↑ "Ethiopia: SNNP region administrative map (as of 15 Aug 2017)" (17 August 2017).
- ↑ Bombe town distance from Addis Ababa and Sodo. https://www.academia.edu/35865257.
- ↑ "Bomibe 01 Town, Boloso Bombe, Wolayita, Ethiopia on the Elevation Map. Topographic Map of Bomibe 01 Town, Boloso Bombe, Wolayita, Ethiopia.".
- ↑ "The 2007 Population and Housing Census of Ethiopia: Statistical Report for Southern Nations, Nationalities and Peoples' Region; Part I: Population Size and Characteristics". Archived from the original on 2022-07-07. በ2025-02-15 የተወሰደ.