ቦረና
Appearance
የቦረና ወረዳ በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከሚገኙ 29ወረዳዎች አንዱ ነው የወረዳውም ዋና ከተማ መካነ-ሰላም ነዉ። የወረዳው አጠቃላይ የህዝብ ብዛት 158,726 ወንድ= 80,040 ሴት= 78,686 ነው፡፡ ወረዳው በ34 ቀበሌዎች የተከፈለ ነው በወረዳው በርካታ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሃብቶች እና የቱሪስት መስህቦች አሉ ፡፡ ከነዚህም መካከል ወንዞች ፣ ተራሮች ፣ ገዳማትና መስጊዶች እንድሁም ለቱሪዝም መስህብ ሊሆን የሚችል የቦረና ሳይንት ብሄራዎ ፓርክ ዋና ዋናዎቹ ናቸው ፡፡ በፓርኩ ውስጥ የተለያዩ በርካታ ዝርያ ያላቸው አእዋፍ ተሳቢና አጥቢ እንስሳት የተሌዩ ዝርያ ያለቸው እጽዋትና አስደናቂ የሆኑ የተፈጥሮ ዋሻዎች ይገኛሉ፡፡
ስልክ ከአዲስ አበባ ያለው ርቀት ከባህር ዳር ያለዉ ርቀት ከደሴ ያለው ርቀት ህዝብ ብዛት ስፋት (ስኩዌር ኪሜ)
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |