ተንታ
የተንታ ወረዳ በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከሚገኙ 24 ወረዳዎች አንዷ ስትሆን የወረዳዋ ርእሰ ከተማ አጅባር ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምስራቅ 529 ኪ/ሜ እና ከክልሉ ዋና ከተማ ባህር ዳር 610 ኪ/ሜ እንዲሁም ከዞኑ ዋና ከተማ ደሴ 128 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡አጠቃላይ በወረዳዋ አምስት /5/ የከተማ ና ሰላሳ ሁለት /32/ የገጠር ቀበሌዎች ይገኛሉ፡፡ በወረዳው 2 መሪ መዘጋጃ ቤትና 3 ንዑስ መዘጋጃ ቤቶች ይገኛሉ፡፡ የወረዳው አዋሳኞች በሰሜን ከአምባሰልና ከደላንታ ወረዳ ጋር በደቡብ ከለጋምቦ ወረዳ ጋር በምስራቅ ከደሴ ዙሪያና ኩታበር ወረዳ ጋር እንዲሁም በምእራብ ከመቅደላ ወረዳ ጋር ትዋሰናለች፡፡ የወረዳው አጠቃላይ የህዝብ ብዛት 190,800 ወንድ= 98,196 ሴት= 92,603 ሲሆን ከአጠቃላዩ ህዝብ ውስጥ በገጠር የሚኖሩ ወንድ= 87,788 ሴት= 82,230 ድምር = 170,018 በከተማ የሚኖሩ ወንድ= 10,408 ሴት= 10,373 ድምር = 20,781 123,835 ሄ/ር የሚሸፍን ሲሆን ከዚህ ውስጥ፡- ለእርሻ የዋለው 59,459.1 ሄ/ር፣ ለግጦሽ የዋለው 19,463.15 ሄ/ር፣ በደን የተሸፈነው 19,491.03 ፣ለግንባታ የዋለ 12,844.05 ሄ/ር እንዲሁም ቀሪው 12577.64 ያህሉ ምንም ጥቅም የማይሰጥ ቦታ ነው፡፡ አጠቃላይ የወረዳውን የአየር ሁኔታ ስናይ ቆላማ /33.5%/ ፣ደጋማ /40%/፣ ወይና ደጋ /26.34%/ እንዲሁም ውርጭ /0.16%/. ያሉን ይሸፍናሉ፡፡
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |