አለባቸው ተካ
Appearance
| መረጃ | አካል |
|---|---|
| ስም | አለባቸው ተካ |
| ቅጽል ስም | አለባቸው ተካ |
| የትውልድ ቀን | 1954 ዓ.ም |
| የትውልድ ቦታ | ሰሜን ወሎ ውርጌሳ |
| የሞት ቀን | 1997 ዓ.ም |
| የሞት ቦታ | ጅማ |
| ዜግነት | ኢትዮጵያዊ |
| የቀልድ ዓይነት | |
| ተጽእኖዎች | |
| ያወሩት | |
| ባለቤት | |
| ሽልማት | |
| ድህረ ገፅ |
አለባቸው ተካ
አለባቸው ተካ በ1954 ዓ.ም በሰሜን ወሎ ውርጌሳ የተባለ ትንሽ ከተማ ተወለደ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በወረዳው የተማረ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ደግሞ አዲስ አበባ ላይ ተምረዋል ።ገና በልጅነቱ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት እያለ የኮሚዲያን ሙያ ፍቅር ያደረበት አለቤ ከኢትዮጵያ ወስጥ ምርጥና ዝነኛ ኮሜዲያን ውሰጥ አንዱ ነበር።
በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን [ኢቲቪ] ላይ አለቤ ሾው የተሰኘው ሳምንታዊ ተወዳጅ የመዝናኛ ፕሮግራም በማቅረብ ከማዝናናቱ አልፎ ለተለያዩ የተጎዱ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖቹ ለመርዳት የሚያስተባብር ሾው በመሆኑ በብዙሃኑ ዘንድ የደሃ አባት አስብሎታል።
አለቤ ለዶክመንተሪ ስራ በሄደበት ወቅት ከጅማ 3ዐ ኪ.ሜ መንገድ ላይ በደረሰበት የመኪና አደጋ ጥር 8 ዓ.ም 1997 ዓ.ም በተወለደ በ 44 ዓመቱ በሞት ተለይቶናል።
አለቤ የሁለት ሴቶች እና የአንድ ወንድ ልጅ አባት ነበረ።የቀብር ስነስርዓቱ ከ60,000 ህዝብ በላይ ይህን ጀግናና የደሀ አባት ለመቅበር ተገኝቶ ነበር።