Jump to content

አማራይዜሽን

ከውክፔዲያ

አማራይዜሽን ማለት የአማራ ወጎች፣ ባህል እና ቋንቋ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሌሎች ብሄረሰቦች የበላይ ሆነው የሚታዩበት ሂደት ነው። በንጉሳዊ አገዛዝ ዘመን አማሮች የአማርኛ ቋንቋንና ባህልን በማስፋፋት እና ፖለቲካውን በመቆጣጠር ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድሩ ነበር። የአማራ የበላይነት ከደርግ ዘመን ጀምሮ እስከ 1983 ድረስ ዘልቋል።

በህወሓት የሚመራው ኢህአዴግ የአማራይዜሽንን ሂደት ለማስቆም በህገ መንግስቱ መሰረት የብሄር ፌደራሊዝምን ለመተግበር ሞክሯል። ሆኖም ህገ መንግስቱ የዘለቄታዊ ግጭቶችን መፍታት ባለመቻሉ በብሄረሰቦች መካከል ያለውን ውጥረት ሲባባስ በፋንታው ህወሓት "ከፋፍለህ ግዛ" የሚለውን ስልት በመጠቀም ራሱን አጠናክሯል።

አማራይዜሽን የብሔር የቋንቋና ሀይማኖት ብዝሀነትን ከሚያቀነቅነው ኢትዮጵያዊነት ጋር የተቃረነ ፅንፈኛ አስተሳሰብ ነው።

ተጨማሪ ይመልከቱ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]