Jump to content

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

ከውክፔዲያ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በ1987 ዓ.ም በበኩር ጋዜጣ ስራውን ጀመረ፡፡ በአሁኑ ወቅት በቴሌቪዥን፣በራዲዮ፣ በጋዜጣ እና በዲዲታል ሚዲያ አማራጮች ዘገባዎችን እያደረሰ የሚገኝ የመንግስት የሚዲያ ተቋም ነው፡፡

ዋና መስሪያ ቤቱን በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ ያደረገው ኮርፖሬሽኑ ደጎንደር፣ደሴ፣ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ እና አዲስ አበባ የኤፍኤም ጣቢያዎችን እና የቴሌቪዥን ስቱዲዮ ግንባታዎችን በማከናወን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

ሚዲያው የምልክት ቋንቋን ጨምሮ በ12 ሃገራዊ እና አለም አቀፍ ቋንቋዎች ዘገባዎችን ያደርሳል፡፡[1]

  1. www.ameco.et