አባል:ሴንት
Appearance
ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በከሰም ወረዳ ልዩ ሰሙ ውቢት በሚባለው ሥፍራ፣ ከታወቁት አባታቸው ከአቶ በላይነህ ቢተውልኝ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ማናለብሽ በድሉ መስከረም ፮ ቀን ፲፱፻ ዓ.ም ተወለዱ። በተወለዱ በአሥራ አምስት ዓመታቸው በቤተ መንግሥት የዕልፍኝ አሽከር ሆነው ሲያግለግሉ ከቆዩ በኋላ ጥንታዊ የክብር ዘበኛ ሲቋቋም በወታደርነት ተዛውረው አግልግሎታችውን አበረከቱ።