Jump to content

አባል:ዛውል ሓማሴን

ከውክፔዲያ

የወንጀል ቅጣት አወሳሰን  መግቢያ ወንጀልን እና ቅጣቱ አብሮ የሚነሳው የቅጣት አወሳሰኑ እንዲሁም የወንጀል ህጉ አላማ ነው፡፡  ቅጣት ሲጣል ወንጀለኛ ዳግም ወደ ወንጀል እንዳይመለስ እና ሌሎችም ከተቀጪው ተምረው ራሳቸውን ከወንጀል ድርጊት እንዲቆጥቡ በማስተማር እና ማስጠንቀቂያ እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡ የወንጀል ህግ አላማ ወንጀል እንዳይፈጸም መከላከል ሲሆን ይህም ስለወንጀል ድርጊቶች እና ስለሚያስከትሉት ቅጣቶች አስቀድሞ በማሳወቅ ስለወንጀል ያለ ግንዛቤ መጨመር ነው፡፡ ወንጀል ተፈጽሞ ሲገኝ ለሌላው ትምህርት እንዲሆን አስተማሪ የሆነ ቅጣትን በመቅጣት አላማውን የሚያሰካ በመሆኑ የሚጣለውም ቅጣት ወጥነት፣ ትክክለኝነት፣ ተገማችነት፣ ምክንያታዊ እና ፍታዊ መሆን አለበት ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ ፍርድ ቤቶች ቅጣትን ሲወስኑ በተመሳሳይ ጉዳዮች ተመሳሳይ ቅጣት በመወሰን የፍርድ ተገማችነትን ማምጣት አላማን ከግምት በማስገባት ነው፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የምናየው የቅጣት አወሳሰን ላይ የአቃቤ ህግ ሃላፊነት እና ሚና፣ የቅጣት አወሳሰን መነሻ እና መድረሻ ሃሳቦች፣ የሞት ቅጣት ቀሪ መሆን አለመሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ሀሳብ ነው፡፡

በቀደምት ታሪክ የተጀመረው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ሲሆን እሱም በባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ኮድ (የሃሙራቢ ህግ/ኮድ)ውስጥ  አይንን ላጠፋ አይኑ ይጥፋ፣እጅ ለቆረጠ እጁ እንዲቆረጥ የሚል ህግ ነው፡፡ አሁን ከወንጀል አድራጊ የወንጀል ማድረግ መነሻ ሀሳብ ተነስተን ከግዜ ወደግዜ የወንጀል ህግ አላማ እና ግብ እያደገ መጥቷል፡፡ በ1996 አ.ም በወጣው የወንጀል ህግ አላማው ለጠቅላላው ጥቅም ሲባል የሀገሪቱን መንግስት የነዋሪዎችን፣ የህዝቦችን፣ የህብረተሰቡን ሰላም፣ ደህንነት፣ መብት እና ጥቅም ማስጠበቅ እና ማረጋገጥ ነው፡፡ ከዛም ይህንን አላማ ለማሳካት ወንጀል እንዳይፈፀም መከላከልን ግብ በዋነኛነት የያዘ ነው፡፡ ስለወንጀል ግንዛቤ በመፍጠር እና ማስጠንቀቂያ በመስጠት ከመከላከል ባለፈ ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝ ደግሞ ወንጀል ፈፃሚውን በመቅጣት ወንጀለኛውን ከሌላ ወንጀል ድርጊት መፈፀም እንዲቆጠብ በማድረግ እና ህብረተሰቡን ከወንጀለኛው እንዲማር ሌላ ተጨማሪ ወንጀል እንዳይፈፀም የማድረግ አላማ ነው፡፡ ወንጀል አድራጊዎች ተቀጥተው ከጥፋታቸው ተምረው እና ታርመው ጥሩ ዜጋ እንዲሆኑ ማድረግ ነው፡፡

በቀደምት ታሪክ የተጀመረው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ሲሆን እሱም በባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ኮድ (የሃሙራቢ ህግ/ኮድ)ውስጥ  አይንን ላጠፋ አይኑ ይጥፋ፣እጅ ለቆረጠ እጁ እንዲቆረጥ የሚል ህግ ነው፡፡ አሁን ከወንጀል አድራጊ የወንጀል ማድረግ መነሻ ሀሳብ ተነስተን ከግዜ ወደግዜ የወንጀል ህግ አላማ እና ግብ እያደገ መጥቷል፡፡ በ1996 አ.ም በወጣው የወንጀል ህግ አላማው ለጠቅላላው ጥቅም ሲባል የሀገሪቱን መንግስት የነዋሪዎችን፣ የህዝቦችን፣ የህብረተሰቡን ሰላም፣ ደህንነት፣ መብት እና ጥቅም ማስጠበቅ እና ማረጋገጥ ነው፡፡ ከዛም ይህንን አላማ ለማሳካት ወንጀል እንዳይፈፀም መከላከልን ግብ በዋነኛነት የያዘ ነው፡፡ ስለወንጀል ግንዛቤ በመፍጠር እና ማስጠንቀቂያ በመስጠት ከመከላከል ባለፈ ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝ ደግሞ ወንጀል ፈፃሚውን በመቅጣት ወንጀለኛውን ከሌላ ወንጀል ድርጊት መፈፀም እንዲቆጠብ በማድረግ እና ህብረተሰቡን ከወንጀለኛው እንዲማር ሌላ ተጨማሪ ወንጀል እንዳይፈፀም የማድረግ አላማ ነው፡፡ ወንጀል አድራጊዎች ተቀጥተው ከጥፋታቸው ተምረው እና ታርመው ጥሩ ዜጋ እንዲሆኑ ማድረግ ነው፡፡ እድሜ አንፃር ስንመለከት፡- ሰዎች በእድሜያቸው መጠን ስለወንጀል ምንነት እና አፈፃፀም ያላቸው አረዳድ በእደሜያቸው ልክ የተለያየ እንደመሆኑ ቅጣትም ለመጣል እንዲሁ ይለያያል፡፡ የወንጀል ህጉ የወንጀል አድራጊን ከማስተማር እና የቅጣት አጣጣል ምጣኔን ለማምጣት ሲባል የወንጀል አድራጊዎችን በእድሜ ለይቶቷቸዋል፡፡ ይኸውም በሶስት የእድሜ ክልል የሚከፍለው ሲሆን፡- ከዘጠኝ (9) አመት በታች የሆኑትን ህፃናት በወንጀል ፍፁም ሊጠየቁ የማይችሉ፣ ከዘጠኝ(9) አመት እስከ አስራአምስት አመት(15) ዕድሜ ያሉት የጥንቃቄ እርምጃ (አንድ ቦታ ተወስነው እንዲቀመጡ፣የፀባይ ማረሚያ ቦታዎች እንዲሄዱ፣የተወሰኑ ቦታዎች ከመሄድ እንዲከለከሉ ማድረግ…) ሲሆን ይህ ቅጣት ውጤት ካላመጣ በስተቀር የገንዘብ ወይም የእስራት ቅጣት ሊቀጡ አይችሉም፣ ከአስራአምስት (15) አስከ አስራ ስምንት (18) አመት የሆኑት በመደበኛ ቅጣት የሚቀጡ ናቸው፡፡

የሞት ቅጣት ክቡር የሆነዉን የሰውን ህይወት የሚያሳጣ የቅጣት አይነት ከመሆኑ የተነሳ ሁለት ተቃራኒ አቋሞች ያሉትና በብዙ መንግስታት እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሀገራት አከራካሪ ነው፡፡ ከሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪዎች አንጻር የሚነሳ ሲሆን ሀሳባቸውን ሲገልፁ በህይወት የመኖር መብት በተፈጥሮ የተሰጠ የማይገረሰስ መብት እንደመሆኑ በፍርድ ሂደት ሊነፈግ አይችልም፡፡ የወንጀል ህጉ አላማ የወንጀል አድራጊን ማስተማር እና ማረም እንደመነሻ ያስቀመጠ በመሆኑ በሞት ቅጣት ወንጀል አድራጊን የሚያርም ሆነ የሚያስተምር አይደለም፣ በሞት ቅጣት ምክንያት ህብረተሰቡ ከወንጀለኛው ተምሮ ወንጀል ማስቀረት(መቀነስ) ይቻላል ቢባልም ተሟጋቾቹ እንደሚያነሱት የሞት ቅጣት በነበረበት ወቅት እና ባልነበረበት ወቅት ያለው የወንጀል መፈፀም መጠን ያልቀነሰ እና ልዩነት የሌለ በመሆኑ የሞት ቅጣት የሚያመጣው የተሻለ ለውጥ ባለመኖሩ ሊቀር ይገባል፣ ሌላው መከራከሪያ በሞት ቅጣት ከተቀጣ በኋላ ስህተት መሆኑ ቢታወቅ ወደኋላ የሚመለስ ባለመሆኑ የማይስተካከል ስህተት ይሆናል የሚሉ ሃሳቦች ያሉ ሲሆን በአንፃሩ ደግሞ የሞት ቅጣትን የሚደግፉት በሕይወት የመኖር መብት ተፈጥሮአዊ መብት ቢሆንም በከባድ ወንጀሎች አማካኝነት ግን የሞት ፍርድ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ከተፈፀመው ወንጀል አንፃር ተመጣጣኝ ቅጣት እስከሆነ ድረስ የወንጀል ህጉም እንደቅጣት ስካስቀመጠው ድረስ እና ሌሎች ከወንጀል ድርጊት እንዲቆጠቡ እስካደረገ ድረስ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል የሚሉ ናቸው፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ በወንጀል ህግ የሞት ቅጣት የሚወሰነው ከባድ ለሆኑ ወንጀሎች እንደሆነ ከድንጋጌው ዝርዝር ሀሳብ ውስጥ አካቷል፡፡ የሞት ቅጣት ከተወሰነ በኋላ እንዲፈፀም በህገመንግስቱ መሰረት ፕሬዝዳነት መፈረም አለበት፡፡ የሞት ቅጣት በወንጀል ህጉ አንቀጽ 117 (1) መሰረት፡- 1. የወንጀል ድርጊቱ በሞት የሚያስቀጣ ስለመሆኑ ወንጀሉን በሚያቋቋመው የህጉ ልዩ ክፍል በግልጽ ተደንግጎ ሲገኝ፣ 2. ወንጀሉ ፍፃሜ ያገኘ ማለትም በሙከራ ደረጃ ላይ ያልተገታ ሲሆን፣ 3. ቅጣቱን የሚያቀልለት ምንም አይነት ማቅለያ ምክንያት የሌለ እንደሆነ፣ 4. የተፈፀመው ወንጀል እጅግ በጣም ከባድና ወንጀለኛው በተለይ አደገኛ ሲሆን እና 5. አጥፊው የቅጣት ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜ እድሜው 18 የሞላዉ ከሆነ ነዉ፡፡

በኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ