Jump to content

አባል:Hawareyawe

ከውክፔዲያ
                                                 አፍሪካዬ
 የሰጪ ተመልካች የመጽዋት ለማኝ 

ሀብት እያለሽ ቤትሽ ልመና የቆምሽ ሌላው አንቺን በልቶ በምግብሽ ሲፋፋ አንቺ ግን ተራቁተሸ ውድተትሽ ሲከፋ ዝምታው ምንድነው ምነው ቁጭት የለሽ አፍሪካ አህጉራችን ለምን አንቀላፋሽ

ምግብሽ ጥይት ሆኖ ቀለብሽ በሽታ 

ግብርሽ የሰው ልጅ ደም ሙዚቃሽም ዋይታ የረሀብ መጋረጃ ሁሌ ተጋርዶብሽ ከላይሽ የማይወርድ የለበሽው ማቅሽ ልባቸው ሸፍቶ በስደት ልጆችሽ ሳይጠሉሽ እርቀው እንጀራ ቢያጡብሽ ምነው የማታዝኚ ምነው ዝም ትያለሽ ልጆችሽ እርስ በእርስ ሲጨፋጨፉልሽ

አምላክ በተፈጥሮ ምንም ሳይበድልሽ ሁሉንም በየዓይት ለአንቺ ቢያስታቅፍሽ በተሰጠሸሸ ጸገጋ መጠቀመም አቀቅተቶሸሽ ምንጭ እያለ ስርሽ ወደ ላይ አንጋጠሸ ወንዙ ሞልቶ ፈሶ ዝናብ የለም እያልሽ ወዘናሽ ጠውልጎ በረሀብ ትፈጃለሽ

ሥጋሽ ላይሽ አልቆ በአጥንትሽ እየኖርሽ


                   አፍሪካዬ......

በለመለመው መስክ ጎጆውን ቀልሰው ኩልል ካለው ውሃ በፍቅር ጠጥተው መኖር ተስኖአቸው ልጆችሽ ተሳስበው ከሰላሙ ሜዳ ጉድጓድ ጫካ መርጠው ይሸልሉልሻል ጀግንነት መስሎአቸው የወንድማቸውን ሬሳ እረግጠው

           እናም አፍሪካዬ...

ነዳጅና ወርቁ ሞልተ ጎተራዬ እያልሽ ብታወሪ ካልታየብሸ ፍሬ ሁሉ አለኝ ብትይ የተፈጥሮ ጸጋ አየሬ የሚስማማ ቆላውና ደጋ እኛ ግን ያየነው ባሩድ ያቃጠለው ቦንብ የዘነበበት ገደል ተራራ ነው ከአንገትሽ የማይወልቅ ጌጥሽ መሳሪያ ነው ሁሌ ለማኝ የሆንሽ ታሪክሽ ይሄ ነው

                   ገጣሚ ዲያቆን ተሰፉ ግርማ