1.3
ሳያውቁ በይባላል መኖር ልክ አይደለም፡፡ በግምት የምናወራው ወሬ እንደ ቀልድ ተቀባብሎ ብዙዎች ጆሮ ይደርሳል፡፡ መነሻው ግምት እንጅ እውነት ስላልሆነ ብዙዎችንም ያስታል፡፡ ብዙዎች ሲስቱ ደግሞ በአንድም በሌላም የትውልድ ስነልቦና ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተፅዕኖ ቀላል አይደለም፡፡ ያ ደግሞ መልሶ ራስን ዋጋ ያስከፍላል፡፡ የሰኔና ሰኞ ግጥምጥሞሽ መጥፎ አድርጎ የማሰብ ክስተትም የዚሁ ውጤት ነው፡፡ በአንድ ወቅት በዚህ ወርና ቀን የተፈጠረን አደጋ በተንሻፈፈ መንገድ ለትውልድ የተላለፈ አጉል ልምድ ነው፡፡