Jump to content

አባል:Jemal Getahun

ከውክፔዲያ

ሰኔና ሰኞ አንድ ቀን ቢውሉ ምን ይፈጠራል?

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

---------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ጠይቆ እውነቱ ጋር የማይደርስ ትውልድ ስቶ ያስታል፡፡  ነገርን አጠማዞ ማወቅ ትውልድ ይገድላል፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሳያውቁ በይባላል መኖር ልክ አይደለም፡፡ በግምት የምናወራው ወሬ እንደ ቀልድ ተቀባብሎ ብዙዎች ጆሮ ይደርሳል፡፡ መነሻው ግምት እንጅ እውነት ስላልሆነ ብዙዎችንም ያስታል፡፡ ብዙዎች ሲስቱ ደግሞ በአንድም በሌላም የትውልድ ስነልቦና ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተፅዕኖ ቀላል አይደለም፡፡ ያ ደግሞ መልሶ ራስን ዋጋ ያስከፍላል፡፡ የሰኔና ሰኞ ግጥምጥሞሽ  መጥፎ አድርጎ የማሰብ ክስተትም የዚሁ ውጤት ነው፡፡  በአንድ ወቅት በዚህ ወርና ቀን የተፈጠረን አደጋ በተንሻፈፈ መንገድ ለትውልድ የተላለፈ አጉል ልምድ ነው፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሰኔና ሰኞ የወርና የቀን ስያሜ ናቸው፡፡ ሰኔና ሰኞ የጊዜ ግጥምጥሞሽ ናቸው፡፡ እንዳውም በተቃራኒው ሰኔ አንድ-- ሰኞ ሲሆን ለሀገራችን ገበሬዎች ጥሩ አጋጣሚ ነው ተብሎ ይታመናል፡፡በምክንያቱም የግንቦት ፀሃይ አልፎ  በሰኔ ወር ዝናብ ሲተካ የወሩ መጀመሪያ ቀን በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ሲውል ጥሩ የስራ ሞራል ስለሚያመጣ በገበሬው ይወደዳል፡፡ አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ገበሬ ስለሆነ መልካም ግጥምጥሞሽ ነው፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ስለዚህ ሰኔና ሰኞ ገጠመልን እንጅ አልገጠመብንም፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሀላፊነት መውሰድ ከራስ እንጀምር፡፡ ለልጆቻችንንና ለታናናሾቻችንን በግምት ሳይሆን በመረጃ ነገሮችን እናስተምራቸው፡፡ እንደዚያ ካደረግን ደግሞ ጥሩ ስብዕና ያለውና በራሱ የሚተማመን በግምት ሳይሆን በመረጃ ብቻ የሚያምን ጥሩ  ትውልድ ማስከተል ይቻላል፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሰኔና ሰኞ ወርና ቀን ነው፤ መሽቶ በመንጋት ድግምግሞሽ ውስጥ የሚከሰት ጊዜ፡፡ የጊዜያችን ትርጉም ደግሞ እኛ ነን፡፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የስራችንና የእምነታችንም ውጤት እኛ ነን፡፡ ይህን ቀን በጥሩም ሆነ በመጥፎ ማሳለፍ የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ ቀኑ ግን መሽቶ መንጋቱን ይቀጥላል፡፡ በፈጣሪ ፈቃድ በተፈጥሮ የሚመላለስን ቀን ገጠመብኝ ብዬ አልፈራም፡፡ እንዳውም እንኳንም ገጠመልኝ፡

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]