አባል:Yosefasefaa
Appearance
ሰበር የመረጃ ግብአት ፣
ኢትዮጵያና ሳውዲ በደመወዝ እየተደራደሩ ነው !
- የትናንት ድርድር አልሰመረም
- የዛሬው ድርድር በጉጉት እየተጠበቀ ነው
የኢትዮጵያና ሳውዲ አረቢያ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች በኮንትራት የቤት ሰራተኞች አወዛጋቢ ደመወዝ ዙሪያ ሪያድ ሳውዲ አረቢያ ላይ ድርድር መጀመራቸው ታውቋል። ትናንት የተጀመረው የቤት ሰራተኞች የደመወዝ ድርድር የሰመረ ያልሆነበት ምክንያት ሳውዲዎች ደመወዙን ከ1000 አንድ ሽህ ሪያል ፈቀቅ ሊያደርጉት ባለመቻላቸው መሆኑም ተጠቁሟል። ይህ በመሆኑ ተጨማሪ ድርድር ለማድረግ ለዛሬ መተላለፉ የመረጃ ምንጮቸ የላኩልኝ መረጃ ያስረዳል ።
ድርድሩ ዛሬም የቀጠለ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት የመደራደሪያ ደመወዝ መነሻ 1150 ሪያል ሲሆን በሳውዲ መንግስት በኩል አሁንም ደመወዙን ከ250 የአሜሪካ ዶላር ወይም ከ1000 ሪያል ከፍ ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆናቸው ይጠቀሳል። ሪያድ ላይ እየተደረገ ያለው ድርድር የተመራው በመላከለኛው ምስራቅ ዳይሬክቶሬት በአምባሳደር ሱሌማን ደዴፎ መሆኑ ሲጠቆም የትናንቱ የከሸፈ ድርድር ሪፖርት ሀገር ቤት ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች መቅረቡን የመረጃ ምንጮቸ አስታውቀዋል።
መረጃው የደረሳቸው ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎችም በደመወዝ ላይ ባተኮረው ድርድር ከዚህ በኋላ ጊዜ ማጥፋትና ስምሪቱን ትግበራ ሊጎትተው ስለማይገባ በተቻለ መጠን ድርድሩን መከወን እንዳለባቸው ለተደራዳሪው ልዑክ መሪ ጥብቅ ትዕዛዝ መሰጠቱን የውስጥ አዋቂ ብርቱ መረጃ አቀባዮቸ ገልጸውልኛል ።
ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ ታህሳስ 29 ቀን 2011 ዓም t.me/josilo