Jump to content

አባል ውይይት:Ezu namrud

Page contents not supported in other languages.
ርዕስ ጨምር
ከውክፔዲያ

Heading text

[ኮድ አርም]

negash m 1 ነጋሽ መሐመድ ይገዙ ሐምሌ 16፣ 1958 አልዩ አምባ ተወለደ።ጋዜጠኛ እና አሰራጭ (ብሮድካስተር) ነዉ።በ1981 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመረቀ።ከጥቂት ወራት በኋላ በ1982 ማስታወቂያ ሚንስቴር (በእጣ) ከዚያም ኢትዮጵያ ራዲዮ በአብዛኛዉ ሕዝብ ዘንድ ዜና ፋይል ተብሎ በሚታወቀዉ የዜናና መዋዕለ ዜና ክፍል በነባር ፕሮግራም አዘጋጅነት ተቀጠረ። በተማሪነት ዘመኑ ምኞቱ አስተማሪ መሆን ነበር።ይሁንና ዕውቁ የራዲዮና የቴሌቪዥን ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም ከሚመራው ክፍል ሲመደብ፣የጋዜጠኝነት ሙያ የሚጠይቀዉን ክሒል፣ ዕዉቀት፣ ሥርዓት፣ ኃላፊነትና ሥነ-ምግባር ለማሟላት ብዙ አላዳገተዉም። ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ከዚህ ቀደም ከ100 በላይ የሚጠጉ በጥበብ፤ በመረጃ እና በመዝናኛ ዘርፍ ያሉ ሰዎችን ታሪክ ሲያቀርብ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የነጋሽ መሀመድን የህይወት እና የስራ ገጽ መግለጽ ልንጀምር ነው፡፡

          መሠረት - የንባብ ፍቅር  

በዩኒቨርስቲ ትምሕርቱ የወሰዳቸዉ የኦዶ ቪዥዋል፣ የምርምርና ዘገባ አፃፃፍ (Research and report writing)፣ትርጉም፣የድርሰት አፃፃፍ (Composition) ሥነፅሁፍና ሌሎችም ኮርሶች ለፈጣን ስኬቱ እርሾ ሆነዉታል። ይሁንና «ራዲዮ ማድመጥ የጀመርኩበትን ጊዜ አላስታዉስም።በልጅነቴ እቤታችን ዉስጥ በክብር የሚቀመጡ ሶስት ነገሮች ነበሩ።» ይላል ነጋሽ።«የእናቴ ጌጦች (በአብዛኛዉ የብር) የአባቴ አሮጌ ጠመንጃ (ምናልባት ምንሽር) እና 6 ባትሪ የሚጎርስ ትልቅ ራዲዮ----» መፅሐፍ፣ ጋዜጣና መፅሔት ማንበብ፣ ወቅታዊ ጉዳይ መከታተል የጀመረዉ የ4ኛ ክፍል ተማሪ በነበረወቅ ነዉ።«ጋዜጠኛ ባልሆንም፣ ጋዜጠኛ ከመሆኔ ከብዙ አመታት በፊት የጀመርኩና የወደድኳቸዉን ማንበብ፣ ማድመጥና ወቅታዊ ሐገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችን መከታተል አልተዉም ነበር» ይላል ነጋሽ።» መፅሐፍት መርጦ የማንበብ ችሎታና ፍላጎቱ፣ ቢቢሲን የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ ማሰራጪያ ጣቢያዎችን ማድመጥ፣ News week እና Time የመሳሰሉ መፅሄቶችንና ሌሎች ሊያገኛቸዉ የሚችላቸዉን ጋዜጦችና መፅሔቶችን ማንበቡ አቅጣጫ ጠቋሚ (ኮፕፓስ) ሆኖት፣ ሰፊና ጥልቁን የጋዜጠኝነት ባሕርን በጥንቃቄ ግን በፍጥነት ወደ ትክክለኛዉ መድረሻ ይቀዝፍ ገባ። የመጀመሪያዉ የፋርስ ባሕር ሰላጤ ጦርነት የፈነዳዉ ነጋሽ ሥራ በያዘበት ዓመት ነበር።1982።ወጣቱ ጋዜጠኛ ለሙያዉ፣በጣሙን ዜናን ለማጠናቀር፣ ላቀራረብና አነባበብ ቴክኒኩ፣ለዜና ፋይልም አዲስ ቢሆንም ቀድሞዉ ጣቢያዉን ከተቀየጡትና ረጅም ጊዜ ካገለገሉት የራዲዮ ጋዜጠኞች እኩል፣ ካንዳዶቹም በበለጠ ጥራት፣ ዉበትና ጥልቀት ዘገባዎችን መተርጎም፣ ማጠናቀር፣ መተንተንና ማሰራጭት ችሏል። የዜና ብልትን የመለየት ልዩ ችሎታዉ፣ በሳል የቋንቋ ዕዉቀቱ፣ ድልብ የቃላት ሐብቱ፣ የአረፍተ ነገር አሰካክ ብልሐቱ፣ የሱና የሱ ብቻ የሆነዉ የአነባበብ ቅላጼና ድምፁ ከመጠነኛ የዓረብኛ ዕዉቀቱ ጋር ተዳምረዉ በዚያ ዘመን ብዙዎች ከሚናፍቋቸው ጥቂት የራዲዮ ጋዜጠኞች አንዱ ለመሆን በቅቷል።