አባል ውይይት:Talargachew Tamirat Biru
ርዕስ ጨምርሰላም
2014
By Talargachew Tamirat Biru (Missionary)
taletamirat940@gmail.com
ሰላም
መግቢያ አሁን ባለንበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ዓለም ከየትኛውም ዘመን ይልቅ በሰላም እጦት የተናወጠች የሚትገኝበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። መላው ዓለም ያለ ልዩነት በነውጥና በግጭት ውስጥ ነው። በሰዉ ልጆች ታሪክ ሰዎች ሁሉ ያለልዩነት ሰላምን በብርቱ ተፈልጎ ሰላም ያልተገኘበት ዘመን ቢኖር አሁን እኛ ያለንበት ይህ ዘመን ነው። ከእኛ ከሰው ልጆችም አልፎ ፍጥረት በሙሉ በሰዉ ልጆች ሰላም ማጣት ዋጋ እየከፈለ ይገኛል። ሰላምን ማስጠበቅ የአንድ ወገን የቤት ስራ ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር በራሱ አምሳል የፈጠረው የሰው ልጅ በሙሉ ኃላፊነት ነው። ይልቁንም ሰላምን በማይናጋ ጽኑ መሠረት ላይ ለመመስረትና ለመጠበቅ እንዲሁም ለማስጠበቅ መያያዝንና አንድነት ብሎም በጎ ፈቃድና ትብብር የሚጠይቅ ነዉ። በምድር ላይ ሰላም እንዲመጣም እንዲደፈርስም ምክንያቶች እኛው የሰው ልጆች ነን፡፡ በመጀመሪያ ጊዜ የሰላም መደፍረስ የመጣው በዘፍ 3፡12-13 ላይ ነው፡፡ አዳም በአንድ ጊዜ ፈጣሪ እግዚአብሔርን እና የአጥንቱ ፍላጭ የስጋዉ ቁራሽ የሆነችዉን ሄዋንን ሲከስና የራሱን ሀላፊነት ላለመዉሰድ ሲያመካኝ እናየዋለን። ሄዋን በበኩሏ አለመታዘዟን በእባብ ላይ ስታመካኝ እናያለን። በፈቃዳቸዉ ላለመታዘዝ በመረጡት ጎዳናና ከእግዚአብሔር ይልቅ ሴይጣንን ለማመን በወሰዱት እርምጃ ቅጣት አግኝቷቸዋል። ሆኖም ግን እግዚአብሔር በኤደን ገነት ውስጥ ለሰዉ ልጆች ያቀደዉ ሰላምና ተድላ ተቋረጠ።
ይህ ተፈጥሯዊ ፍጹም የሆነው የእግዚአብሔር ከሰው ልጆች ጋር የነበረው የሰላም ኪዳን ስለተቋረጠ፤ ዓለም ምንም ያህል በስልጣነ ማማ ላይ ቢትቀመጥም፤ የሰላም ፍለጋ ከትላንት ይልቅ ዛሬ እየበረታ መጥቷል። የሰዉ ልጅ ፈጣሪን ባለመታዘዝ በገዛ መንገዱ ለመሄድ ከወሰነበት ቀንና ሰዓት አንስቶ ሰው በጎንዮሽ ግንኙነቱ (ከባንጀራው ጋር)፤ ከፈጣሪው ጋር ያለው ግንኙነቱና ከተፈጥሮ ጋር ያለው ግንኙነቱና ቁሪኝቱ ሰላም ደፍርሷል፤ ግንኙነቱም ተቋርጧል። ሰላም ምንድር ነው?
የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂመብልና መጠጥ አይደለችምና። (ሮሜ 14፡17) ሰላም፡- ለምለው ቃል አንድ ወጥ የሆነ ቀጥተኛ ጥሬ ትርጉም ለመስጠት ያስቸግራል፡፡ ስለዚህ በብሉይ ኪዳን መጽሐፍ በዕብራይስጥ ቋንቋ ‹‹ሻሎም›› የምለውን ቃል ይጠቀማሉ፡፡ እኛም ሰላም እንለዋለን፡፡ ይህን ቃል እያንዳንዱ ግለሰብና ኅብረሰብ እንደየባህሉና እንደየቋንቋው በተለያየ መንገድ ይረዳዋል፡፡
ሰላም የፍጹምነትን፣ የሙላትንና የመልካም ማንነትን ሐሳብ ይዟል፡፡ ሰላም እንደየማህበረሰቡ መረዳት ‹‹የተረጋጋ፤ ፀብና ጦርነት የሌለበት መልካም ጤና፣ ሀብት እና መልካም ግንኙነቶችን የሚያጠቃልል ምሉዕ ቃል ነው፡፡ ሰላም በስምምነትና በአንድነት አብሮ መኖር እንዲሁም ሰዎች ጋር ስንገናኝ በቅድሚ ለሰው መልካም ምኞታችንን፤ መልካም ጤናንና ደስታውን በመመኘት ለሰውዬው ያለንን መልካም ምኞት የሚንገልጽበት ብቸኛ ቃል ሰላም ነው፡፡ ሰላም የንግግር መክፈቻ ቃልም ነው፡፡ (ዮሐ 20፡19) ስለዚህ ሰላም መንፈሳዊና አካላዊ ወይም ሁለንተናዊ ደኅንነት እና ሁለመናዊ ድነት የሚለውን ጠንካራ መልዕክት የያዘ ቃል ነው፡፡ እስራኤላዊያን ከአሮን ቡራኬ ውስጥ ስለሰላም በመንፈሳዊ መላኩ ከአምላካቸው ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ አንድነት መፍጠር ሲያስቡ በምድራዊ ኑሮአቸው ደግሞ ስለግለሰብ አእምሮአዊ፤ መንፈሳዊ፤ አካላዊና ሥጋዊ ማንነት፤ ሰላም ደግሞ ስለኅብረተሰብ የርስ በርስ መልካም ግኑኘነትና እንዲሁም ከተፈጥሮ ጋር ካላቸው ጤናማ ኑሮ ጋር ጭምር በማያያዝ ይረዱታል፡፡ (ዘኁል 6፡26) በአጠቃላይ ሰላም የሚለው ፅንሰ ሐሳብ ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር፤ ከርስ በርሳቸው ጋር፤ ከራሳቸው ጋርና ከተፈጥሮ ጋር በስምምነትና በአንድነት በጣምራ አብሮ መኖርን ያመለክታል፡፡ (ሮሜ 5፡1፤ ቆላ 1፡2፤ ኤፌ 2) ሰላምን እንዲሆን የሰዎች መሻት
የሰው ልጅ ሰላምን ይሻል፡፡ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት እንደሆነም ይረዱታል፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ሰላምን በመፈለግ ላይ ነዉ። ስለ ሰላም ብዙዎች ዘምረዋል፤ በርካቶችም ጽፈዋል፤ ብዙዎች ስለ ሰላም ብለው ህይወታቸውን መስዋዕት አድርገዋል። ሰላም ለማቆየት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ይበልጡን የሰላም እጦት ሊያጋጥም ይችላል፡፡ ሰላምን ፍለጋ ብዙዎች መንፈሳዊ ጉዞዎች አድርገዋል። ሌሎች ደግሞ ሰላምን ሲፈልጉ የሱስ ተጋላጭ ሆነው ይበልጥ ሰላማቸውን አጥተዋል። በዓለም ላይ የሚገኙት ሀይማኖቶችም በአንዱ ወገን አምነታችን የሰላም ሀይማኖት ነው ይላሉ፤ በሌሎች ደግሞ የእምነታችን ራስ የሰላም አለቃ ኢየሱስ ነው ይላሉ። በዓለም አደባባዮች መንግስታትና ሀገራት የሰላም ማስጠበቅ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል። በርካታ የሰላም ኮንፈራንሶችም ተደርገዋል፡፡ የሰላም አምባሳደሮችም በየዓለም ሀገራቱ ተሸመዋል፡፡ ስለሰላም የሠሩትንም ለማበረታታት ሁገራት ይሸልማሉ፡፡ ሁሉም የዓለም ሀገራት ለሰላም ከፍተኛ በጄት ይመድባሉ፡፡ ሰላምን በብርቱ ይፈላጋሉ፡፡
ነገር ግን የዓለም ሀገራት ስለሰላም የተፈራረሙት ፊርማቸው ሳይደርቅ ለግጭት የተጋበዙ፣ የአደራዳሪና አስታራቂ ሽማግሌም የጠሩም በርካቶች ናቸው። ሰላምን ለማጽናት የሰላም ሚኒስቴር እስከማቋቋም ተደርሷል። ሀገራት አንዳንድ ጊዜ ሰላምን የጦር መሳሪያ በመታጠቅ ሊያስጠብቁም ይሻሉ፡፡
ለሰላም መታሰቢያነት አርማዎች በእርግብ ምስል ከአገራት ባንዲራ ጎን ለጎን ተውለውልበዋል። ይሁን እንጂ የሰላም መጥፋት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። መነሻ ምክንያቱም ከወትሮው ቀላልና ለመፍታት ዉስብስብና አስቸጋሪ እየሆነ መጥቷል። አሁን አሁን ሰላምን ከማግኘት ይልቅ ሰላምን ማጣት ለሰው ልጆች ቀላል እየሆነ መጥቷል።
የሰው ልጅ በምድር እየበዛ በመሄዱ ምክንያት የሀጢያት መረብ ከመቼውም ይልቅ ውስብስብና ለመበጠስ እስካይቻል ድረስ ጠንካራ አድርጎታል። እግዚአብሔርም ሰዉን በመፍጠሩ ሲፀፀት እናየዋለን።
ሰላም የእግዚአብሔር መገኘት መገለጫም ነው
ይህም ሆኖ በአሁኑ ዘመን ቢሆን የእግአብሔር ስሙ በተጠራበት ቦታ ሁሉ ስለቅዱስ ስሙ ሲል ይገኛል፡፡ ወደ እግዚአብሔር መመለስ እንደ ቃሉ መኖርና የቀደመውን ፍቅር መፈለግ ነው፡፡ በመመለስ መታደስ የመንፈሳዊ ተሐድሶ ዓይነተኛ ባሕርይ እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል በክብር መገኘት ነው፡፡ ቤተክርስትያን ስትታደስ እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል ይገኛል፡፡ እግዚአብሔር ከመገኘቱ የተነሳ በሕዝብ መካከል ፍቅር ይበዛል፤ አንድነት ይጠነክራል፤ አንድ የሚያደርገን የእግዚአብሔር ክብር ነውና፡፡ ስለዚህ መታደስ የሚሆነው እግዚአብሔርን በማወቅ በማክበር በመፍራት እርሱን እንደ ቃሉ በመከተል ነው፡፡ የሚያድስ የእግዚአብሔር መንፈስ ነው፡፡ መታደስ የሚመጣው በመመለስ ነው፡፡ ንስሐ መታደስን ይቀድማል፡፡ (2ዜና 7፡14)
የእግዚአብሔር ሕዝብ ከክፉ መንገዱ ሲመለስ ለምድር መፈወስና በረከት ምክንያት ያሆናል ምድራችን አፈሯ ሊፈወስ ልትባረክ የሰላም ምድር ልትሆን ያስፈልጋታል፡፡ ይህ የምድር መፈውስ ነው፡፡ ፈዋሹ ‹‹ሕዝቤ›› ብሎ የሚጠራው የራሱን ሕዝብ ፀሎት ሰምቶ ለመመለስ ነው፡፡ በአንዳንድ አካባቢ የፍቅር መቀዝቀዝ ዓለምን የመመስል፤ እርስ በርስ መጠላላት መካሰስ ወንጌል ላልሰሙት ለማድረስ ትጋት መቀነስ ይታያል፡፡ ስለዚህ ጣፋጩ ምንጭ ደፍርሷል የእግዚአብሔር ስሙ አልተከበረም በቤቱ መገፋፋት ይታያል፡፡ በእኛ ምክንያት ብርሃኗ ከእንቅብ በላይ አልሆነም ጣፋጭ ምንጭ ነበረች ጣፋጭ የነበረው ምንጭ እንዴት ደፈረሰ እንዴትስ ረከሰ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ማረን ይቅር በለን አሁን በሕዝብ መካከል የማታየውን ነውር ሁሉ አስወግድልን ቤተክርስትያን ከምድር እርግማንን ለማሻር ጭንገፋን ለማቆም መራራውን እንዲጣፍጥ ለማድረግ በእግዚአብሔርና በምድሪቱ መካከል በመሆን የእግዚአብሔር ባሕርዩንና መልካምነት ለሕዝቡ የማታስታውቅ ለምድሪቱም የሚትማልድ ነች፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ በስሙ የተጠራውን ሕዝብ ፀሎት ከሰማይ ሆኖ ይሰማል ምድርቱንም ይፈውሳል፡፡
ሰላም የመንፈስ ፍሬ ነው፡፡ ገላ 5፡22 የመንፈስ ፍሬ በአንድ አገር ሕዝብ መካከል ቢታይ ኖሮ ያች ሀገር የሰላምና የፍቅር ምድር በሆነች ነበር! መንፈሳዊ አንድነት የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው፡፡ (1ቆሮ 12፡12-13) የመንፈስ አንድነት ባለበት ሰላም አለ፡፡
አማኞች ከሌሎች ሰዎችና ከራሳቸው ጋር በሰላም እንዲኖሩ ታዝዘዋል ሮሜ 12፡18 1ጴጥ 3፡11
ሰላምን እንዴት ማምጣት እንችላለን?
ቤተክርስትያን የእግዚአብሔር ዓይንና ጆሮ ሆና የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ ማገልገል ይገባታል፡፡ የቤተክርስትያን ተቀዳሚ ተግባር የምሥራች ቃል ከመሰበክና ከመፀለይ እያንዳንዱ አማኝ በጨለማ በተያዘው ዓለም ውስጥ ብርሃን ሊሆን ይገባል፡፡ ስለዚህ ምስክርነታችንን የምንሰጥበት የመጀመሪያው መንገድ ኑሮአችን ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹በመጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ›› በማለት ለኤፌሶን ቤተክርስቲያን ይናገራል፡፡ ኤፌ 4 ለሕዝባችን አንድ ጌታ አንድ መንግሥት አንድ አገር አንድት ከተማ አላቸው በሕዝብ መካከል ምንም ዓይነት የዘርና የወገን ወይም የደረጃ ልዩነት ሳይኖር ሁሉም እኩል የእግዚአብሔር ልጆች የአዳም ዘር ናቸው፡፡ ገላ 3፡26-28 ቲቶ 3፡5-7
1. ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ
’’… እግዚአብሔር ህዝቡን በሰላም ይባርካል፡፡’’ (መዝ 29፡11) የሰላም ሁሉ ምንጭ እግዚአብሔር ብቻ እንደሆን ሊንታመንበት ያስፈልጋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ’’… እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።’’ ይላል፡፡ (መዝ 127፡1) እግዚአብሔር ከተማችንን ሀገራችንንና ካልጠበቀ በሰላም ሊንመላለስ አንችልም፡፡
2. ከእግዚአብሔር ጋር በመስማማት
’’አሁንም ከእርሱ ጋር ተስማማ፤ ሰላምም ይኑርህ፤ በዚያም በጎነት ታገኛለህ፡፡ ’’ (ኢዮ 22፡21)
ከእግዚአብሔር ጋር መስማማት ማለት እግዚአብሔር ሕዝቡ እንዲኖርለት በሚፈልገው የሕይወት ደረጃ መኖርና እግዚአብሔር ሕዝቡ እንዲጓዝበት በሚፈልገው የሕይወት መንገድ መጓዝ ማለት ነው፡፡ ‹‹… በሕጌ ይሄዱ ወይም አይሄዱ እንደሆነ እኔ እንድፈትናቸው፥ እነሆ ከሰማይ እንጀራን አዘንብላችኋለሁ፤ ሕዝቡም ወጥተው ለዕለት ለዕለት የሚበቃቸውን ይልቀሙ።›› (ዘጸ 16፡4) እግዚአብሔር እስራኤላዊያን ሁሉን በሚችል አምላክ የሆነውና የሚመራቸውም እርሱ ከሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ እንደማያሳጣቸው ወይም እንደማያጎድልባቸው በእርሱ የታመኑ እንዲሆኑ ይፈልግ ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር መስማማት ሰላምና ደስታን ይሰጣል፡፡ ምንም በማትመች ምድር ላይ ቢንኖርም በዚህ በእንግድነት ኑሮአችን እፎይታን እናገኛለን፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ስንስማማ በጎ የሆነውን ነገር እናገኛለን፡፡
እንግዲህ ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት እንስማማለን? በምንስ እንስማማለን? ትሁታን ስንሆን የሰላም አለቃ ኢየሱስ ክርስቶስ አብሮን ይሆናል፡፡ እርሱ ከእኛ ጋር ካለ ሰላም አብሮን አለ ማለት ነው፡፡፡
2.1. ሕጉንና ትዕዛዛቱን በመጠበቅ ‹‹በትእዛዜም ይሄዱ ዘንድ ፍርዴንም ይጠብቁና ያደርጉ ዘንድ አንድ ልብ እሰጣቸዋለሁ፥ በውስጣቸውም አዲስ መንፈስ እሰጣለሁ፥ ከሥጋቸውም ውስጥ የድንጋዩን ልብ አወጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣቸዋለሁ፤ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ።›› (ሕዝ 11፡20-21) ‹‹በመንገዱም እንድትሄድ እርሱንም እንድትፈራ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቅ።›› (ዘዳ 8፡6) ኢየሱስ ትሁት ነበር፡፡ (ዘካ 9፡9፤ ማቴ 11፡29)
2.2. በትህትና በመኖር ‹‹ሰው ሆይ፥ መልካሙን ነግሮሃል፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ፥ ምሕረትንም ትወድድ ዘንድ፥ ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሄድ ዘንድ አይደለምን?›› (ሚክ 6፡8) በምድር ሲንኖር እንደክርስቲያን ለመኖርና ለመመላለስ ትህትና ያስፈልገናል፡፡ ትህትና እግዚአብሔርን ከሰዎች ጋር በቅርበት እንዲገናኝ፤ የእግዚአብሔርን ኃልዎት ይስባል፡፡ ያለ ትህትና እግዚአብሔር አይገኝም፡፡ ‹‹ሙሴም በምድር ላይ ካሉት ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት ሰው ነበረ። … እግዚአብሔርም … ባሪያዬ ሙሴ ግን እንዲህ አይደለም፤ እርሱ በቤቴ ሁሉ የታመነ ነው። እኔ አፍ ለአፍ በግልጥ እናገረዋለሁ፥ በምሳሌ አይደለም፤ የእግዚአብሔርንም መልክ ያያል፤ በባሪያዬ በሙሴ ላይ ትናገሩ ዘንድ ስለ ምን አልፈራችሁም? አለ።›› (ዘኁ 12፡3-7) እግዚአብሔር ከትህታን ጋር ይነጋገራል፡፡ ‹‹እነዚህን ሁሉ እጄ ሠርታለችና እነዚህ ሁሉ የእኔ ናቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን ወደዚህ ወደ ትሑት፥ መንፈሱም ወደ ተሰበረ፥ በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ።›› (ኢሳ 66፡2) እግዚአብሔር ለትሁታን ጸጋን ይሰጣል፡፡
ትህትና የሰላም መሠረት ነው፡፡ ያለትህትና ሰላምን ለማምጣት መሞከር ከንቱ ምኞት ነው፡፡ ትህትና የሰዎችን ልዩነቶች ተቀብለን አብረን እንዲንኖር ያደርገናል፡፡ ልዩነታችን ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን ስጦታ ተቀብሎ እርስ በርስ ለማገልገል እንኳ ትህትና ያስፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር ሲፈጥረን የተለያዩ ሰዎች አድርጎ ነው የፈጠረን፡፡ ሁላችንም የተለያየ አስተሳሰብ፣ አመለካከት፣ ስጦታ፣ ዝንባሌና ፍላጎት ያለን ሰዎች ነን፡፡ በእኛ ውስጥ ስላለው ትክክል ነው ብለን ስለምናምነው አስተሳሰብ፣ አመለካከት፣ ስጦታ፣ ዝንባሌና ፍላጎት ንስሃ እንደማንገባ ሁሉ ሌላውም ሰው በውስጡ ስላለው አስተሳሰብ፣ አመለካከት፣ ስጦታ፣ ዝንባሌና ፍላጎት ማንንም ይቅርታ ባይጠይቅ መገረም የለብንም፡፡ ይህ የተፈጥሮ ጉዳይ ነውና፡፡ ልዩነቶቻችንን ለመቀበል ትህትና ያስፈልገናል፡፡ ልዩነቶቻችን በትህትና ካልተቀባበልን ለግጭቶችና ለሰላም መደፍረስ መንስኤ ይሆናል፡፡ ስለዚህ በትህትና እንመላለስ፡፡ ስለ ሰላም ስባል ትሁታን እንሁን!
2.3. ሌሎችን በመውደድ ‹‹እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።›› (ማቴ 5፡44-45) ‹‹… ባልንጀራህንም እንደ ነፍስህ ውደድ›› (ማቴ 22፡39)
3. በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በመታመን ‹‹ተራሮች ይፈልሳሉ፥ ኮረብቶችም ይወገዳሉ፤ ቸርነቴ ግን ከአንቺ ዘንድ አይፈልስም የሰላሜም ቃል ኪዳን አይወገድም፥ … የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።›› (ኢሳ 54:10-13) ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ሰላም በምናየዉ በገሀዱ ዓለም ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ላይ የተመሠረተ ነው። ስለዚህ ውስጣዊ ሰላም ከአእምሮ ስሌት፣ ከልብ ሀሳብ የሚያልፍ ነዉ። ከእግዚአብሔር ዘንድ ያልሆነ (የዓለም ሰላም) ጊዜያዊ ነው፡፡ ዛሬ ታይቶ ነገ ይጠፋል፡፡ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚናገኘው ሰላም ለልጅ ልጅ ነው፡፡
4. ኢየሱስ ክርስቶስ በሚሰጠን ሰላም ተስፋ በማድረግ
ኢየሱስ የሰላም ምንጭ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የሰላም ምንጭ ብቻ ሳይሆን የሰላም አለቃ ነው። (ኢሳ 9፡6)፡፡ እርሱ የሰላም አለቃ ከሆነ ያለኢየሱስ ሰላም የለም ማለት ነው፡፡ ስለዚህም ነው መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹እርሱ ሰላማችን ነው፡፡›› በማለት የሚተርክልን፡፡ (ኤፌ 2፡14) ሰላም ያለኢየሱስ የለም፡፡ ደግሞም ኢየሱስ ክርስቶስ የሚሰጠን ሰላም የሚጠፋ ወይም የሚደበዝዝ አይደለም፡፡ ከምድር ወይም ከጥረታችን የሚናገኘው ሰላምም አይደለም፡፡ በሐብት፣ በገንዘብ ወይም በሰዎች ዘንድ ዕውቅናን በማግኘት የሚናገኘውም ሰላም አይደልም፡፡ ኢየሱስ የሰጠን ሰላም እንደወንዝ የሚፈስ ሰላም ነው፡፡ በእርሱ ከታመንን ይህንን ሰላም ማንም ልወስድብን አይችልም፡፡
በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል የሆነው ሰላም ምድራዊና የሚጠፋ ሳይሆን አዕምሮን ሁሉ የሚያልፍ፤ ከመረዳትም ያለፈ የውስጥ ሰላም ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ’’አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።’’ ተብሎ ተጽፏል፡፡ (ፊልጵ 4፡7)
ኢየሱስ ክርስቶስ ከአዳማዊ ማንነት የተገነባውን የጥልን ግድግዳ በሥጋዉ አፍርሷል። በአዳም ዘርና በእግዚአብሔር መካከል ፈርሶ የነበረዉን የግንኙነት መስመር በመስቀሉ ሥራ ተገንብቷል። በመስቀል ላይ በተሰራልን ሥራ ከእግዚአብሔር ጋር ታርቀናል፤ ሰላምም ተፈጥሮልናል፡፡ እንግዲህ የጥሉ ግድግዳ ፈርሶ፤ ከእግዚአብሔር ጋር ከታረቅን፤ የማስታረቅንም አገልግሎት ከተቀበልን፤ የሰላም አምባሳደሮች/እንደራሴዎች ነን፡፡ እኛ በእርሱ ሥራ አንድ የሆነን፤ ከጥል ወደ ፍቅር የተጠራን፤ የእርሱን ሰላም በውስጣችን የተሸከምን እኛ ከሌሎች ማህበረሰቦች ጋር በተግባቦትና ጤናማ ግንኙነት ሊንመላለስ ይገባናል። የእግዚአብሔርን ሰላም በኑሮአችን መለማመድ ይኖርብናል፡፡ የሰላሙንም ንጉስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በላያችን ላይ ልናነግስ ይገባል።
5. በምድር ላይ እንግዶችና መጻተኞች መሆናችንን በመረዳት
እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን፤ …፡፡ (ፊልጵ 3፡20)
እኛ እንግዶችና መጻተኞች ነን፡፡ ሀገራችን በሰማይ ነው፡፡ ዜግነታችን ሰማያዊ ነው፡፡ ቤታችንም ዘላለማዊ ነው፡፡ ‹‹ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።›› (2ቆሮረ 5፡1) ሥፍራችንም በላይ በሰማይ በአባታችን በአብ ቀኝ ነው፡፡ ‹‹ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ። በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤ ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።›› (ዮሐ 14፡1-3) ልባችንም ያለው በዚያው ነው፡፡ የኛ የሆነው ባለበት ልባችንም በዚያ ይሆናል፡፡ (ማቴ 6፡19-21)
እኛ ከርስቲያኖች እንግዶችና መጻተኞች የሆንነው የሥጋዊ ኑሮአችን ከሆነው ከሥጋችን ተለይተን ከክርስቶስ ጋር ለዘላለም ከእርሱ ጋር እንደሚንኖር ስለሚናውቅ ነው፡፡ ይህች ምድር የእኛ ዘላለማዊ መኖሪያችን አይደለችም፡፡ ይህንንም ስለሚናውቅ በእንግድነት ለጊዜአዊ ዓላማ በምድር እንኖራለን፡፡ ‹‹ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤ …፡፡›› (1ጴጥ 2፡11) እኛ በምድር ላይ ሲንኖር እንግዶችና መጻተኞች ነን፡፡ ‹‹እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ። እንዲህ የሚሉት ለእነርሱ የሚሆነውን አገር እንዲፈልጉ ያመለክታሉና። ያን የወጡበትን አገር አስበው ቢሆኑ፥ ሊመለሱ ጊዜ በሆነላቸው ነበር፤ አሁን ግን የሚበልጠውን እርሱም ሰማያዊ አገር ይናፍቃሉ። ስለዚህ እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነርሱ አያፍርም፥ ከተማን አዘጋጅቶላቸዋልና።›› (ዕብ 11፡13-16)
በዚህ ኑሮአችን አስቀድመን እንግዶችና መጻተኞች ነን፡፡ ስለዚህ እኛ በምድር የሚንኖረው የእግዚአብሔርን ፈቃድ በምድር ለማከናወን ነው፡፡ ምድርና ሞላዋ የእግዚአብሔር ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ ነው፡፡ (2ቆሮ 5፡18-19) ‹‹ምድርም ለእኔ ናትና፥ እናንተም ከእኔ ጋር እንግዶችና መጻተኞች ናችሁና ምድርን ለዘላለም አትሽጡ።›› (ዘሌ 25፡23) ምድር የእግዚአብሔር ናት፡፡ እኛ በእንግድነት በምድር እንዲንቀመጥ ተናግሮናል፡፡
ሰማያዊ ዜግነት ያለን፤ በዚህች ከንቱ በሆነች ምድር በእንግድነት የሚንኖር ክርስቲያኖች የእኛ ባልሆነ ነገሮችና ጉዳዮች ሊንጣላና ሊንጠላላ አይገባንም፡፡ ‹‹አባቶቻችንም ሁሉ እንደነበሩ እኛ በፊትህ ስደተኞችና መጻተኞች ነን፤ ዘመናችንም በምድር ላይ እንደ ጥላ ናት፥ አትጸናም።›› (1ኛ ዜና 29፡15) ሐዋሪያው ጳወሎስ በዕብ 11፡13-15 ላይ ሰማያዊ ዜግነት ያላቸው አማኞች በምድር ላይ እንግዶችና መጻተኞች ሆነው እንዳሳለፉ ይናገራል፡፡
እንግዲህ ምርጫው የእኛ ነው፡፡ ሁለት ሀገር የለንም፡፡ የሚንኖርላትና የሚንዋደቅላት ሀገር የትኛዋ እንደሆነች ዛሬ ሊንለያ ያስፈልጋል፡፡ በምድር ሀገር በምድራዊ ልብና አስተሳሰብ ኖረን በምድር ለመሞት ወይንም ሰማያዊ ሀገራችንን ተስፋ አድርገን በምድር ላይ እንግዶችና መጻተኞች ሆነን ኖረን ሰማያዊቷንና ዘላለማዊቷን ሀገር መውረስ፡፡ እንደሌሎች ደግሞ ምድራዊቷን ሀገር ዘላለማዊ አድርጎ ማሰብም አታላይነት ነው፡፡ ምድር ዘላለማዊ አይደለችም፡፡
6. ሁላችንም የአንድ አባት ልጆች /የአዳም ዘር መሆናችንን በመገንዘብ
‹‹የአዳም የትውልዱ መጽሐፍ ይህ ነው። እግዚአብሔር አዳምን በፈጠረ ቀን በእግዚአብሔር ምሳሌ አደረገው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፥ ባረካቸውም። ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን አዳም ብሎ ጠራቸው።›› (ዘፍ 5፡1-2) ‹‹እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ፥ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ስፍራ ዳርቻ መደበላቸው። ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።›› (ሐዋ 17፡26-27) የሁላችንም አባት አንድ ነው፡፡ የምንገኝባት የጋራ መኖሪያ ምድራችን የተሰጠችው ለአንዱ አዳም ነው፡፡ አንዱ ወገን የሚኖርባት፣ ሌላው የሚገለልባት አይደለችም፡፡ ሁላችን በጋራ ሆነን በመረዳዳት እና በመዋደድ በሰላም በጤናና በደስታ እንድንኖርባት የተሰጠን ናት፡፡ መረዳዳት ሰላማዊነት ከሰዎች ጋር ብቻ የሚደረግ ሳይሆን በምድሪቱ ላይ ከሚገኙ ከሁሉም ፍጥረታት ጋር ነው፡፡ ሁላችንም የአንድ አባት ልጆች፣ የአንድ ቤተሰብ ልጆች መሆናችንን ማወቅ ይኖርብናል፡፡ የወንድሞቻችንና የእህቶቻችን ሰላም ማጣት የኛም ሰላም ማጣት ነው፡፡ የእነርሱ ስቃይ የሁላችን ስቃይ ነው፡፡ የእነርሱ ደስታና ብልጽግና የሁላችን ደስታ እና ብልጽግና መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
እንግዲህ መጽሐፍ ‹‹በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ …፡፡›› ካለን ሁላችንም ከአንድ አባት መሆናችንን ሊንገነዘብ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ እኛ በሚንኖርባት ምድር ላይ ሆነን ለራሳችን ምን እንፈልጋለን? ያንኑ ለወንድሞችና ለእህቶቻችን እናድርግ፡፡ ሰላም በምድር ላይ እንዲመጣ ከፈለግን በራሳችን ላይ እንዲደረግ የማንፈልገውን ነገር ደግሞ በወንድምና እህቶች ላይ እንዲደረግ መፍቀድ የለብንም፡፡ ‹‹እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው፤ ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና።›› (ማቴ 7፡12) ሌሎች ሰዎች እንዲያደርጉልን የሚንሻውን ያንኑ ለውንደምና እህቶቻችን ሊናደርግላቸው ይገባል፡፡
ሌለው ደግሞ ከአዳም ዘርነት አልፎ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠርን ሰዎች ነን፡፡ ይህም ደግሞ አብረን እንዲንኖር፤ ምድርን እንዲንሞላና እንዲናስተዳድራት በትዕዛዝ የተሰጠን ሰዎች ነን፡፡ እግዚአብሔር ምድርን ሙሉአት ካለን አብረን ተባብረን ምድርን ሞልተን እንዲንኖር እንጂ ተገፋፍተን ሰላምን እንዲናጣ አልታዘዝንም፡፡ ቤቴክርስቲያን ማን ናት
ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆኑ የእግዚአብሔር መንፈስ የሚኖርበት፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥም አምነው የዳኑ፤ የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ የሆኑ በሥሙ የተጠሩ ሰዎች/ሕዝብ ስብስብ ነው፡፡ በ1ቆሮ 3፡17 “… ያውም እናንተ ናችሁ›› ስል የእግዚአብሔርን ሕዝብ ተብሎ የሚጠራ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ዓይንና ጆሮ ሆና የእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ ማገልገል ይገባታል፡፡ የቤተክርስቲያን ተቀዳሚ ተግባር የምሥራች ቃል ከመሰበክና ከመፀለይ እያንዳንዱ አማኝ በጨለማ በተያዘው ዓለም ውስጥ ብርሃን ሊሆን ይገባል፡፡ ስለዚህ ምስክርነታችንን የምንሰጥበት የመጀመሪያው መንገድ ኑሮአችን ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ኤፌ4፡1 ‹‹በተጠራችሁበት በመጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ›› ለሕዝባችን አንድ ጌታ አንድ መንግሥት አንድ አገር አንድት ከተማ አላቸው በሕዝብ መካከል ምንም ዓይነት የዘርና የወገን ወይም የደረጃ ልዩነት ሳይኖር ሁሉም እኩል የእግዚአብሔር ልጆች የአዳም ዘር ናቸው ገላ 3፡26-28 ‹‹በእምንት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም ወንድም ሴትም የለም ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና፡፡ የሰው ልጆች ሁሉ አንድ የሚያደርጋቸው መሠረታዊ አንድነት አላቸው፡፡ይህ እንዳለ ሆኖ የሰው ዘር ስብጥርነት ወይም ፈርጀ-ብዙ ባሕሎች ያሉት በመሆኑ ይህም እርግማን ሳይሆን የሰውን ሕይወት ውብ የሚያደርግና የሚያበለጽግ መሆኑን መረዳትና በአንድነት ልዩነት በልዩነት አንድነት መኖሩን ተረድተን በመከባበርና በመቻቻል መኖር ይተበቅብናል፡፡ይህ ሲሆን ብቻ ነው ሰላም ዕድገትና ብልጽግና ሊመጣ የሚችለው፡፡ ስለዘህ ቤተክርስትያን ባለበት ሰላም አለ፤ ሰላም ባለበት ፍቅር አለ፤ ፍቅር ባለበት እግዜአብሔር አለ፤ አግዚአብሔር ባለበት ሁሉም አለ፡፡
ከጥንት ጀምሮ የታላላቅ ሰዎችን ታሪክ በምናጠናበት ወቅት በዓለማችን ታላላቅ ሥራ በመሥራት በጎ ተጽእኖ ያመጡት ሰዎች የብዙዎች መነሻ ቤተክርስትያን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ቤተክርስትያን የእግዚአብሔር ወንጌል በመስበክ ለሰዎች የደነትን መንገድ አብሳሪ ከመሆኗም ባሻገር የጥሩ ዜጋ መፈጠሪያ መሰሪያና ፍትህ የሚገኘባት ሰፍራም ነች፡፡ሥራዋ ቀጣይነት እንድኖረው በክርስቶስ ፍቅር ውስጥ መኖር ነው፡፡ ሰላምን ለማምጣት የቤተክርስትያን ሚና ምንድ ነው?
ከጥንት ጀምሮ የታላላቅ ሰዎችን ታሪክ በምናጠናበት ወቅት በዓለማችን ታላላቅ ሥራ በመሥራት በጎ ተጽእኖ ያመጡት ሰዎች የብዙዎች መነሻ ቤተክርስትያን ሆና እናገኛለን፡፡ ቤተክርስትያን የእግዚአብሔር ወንጌል በመስበክ ለሰዎች የደህንነትና የሰላም መንገድ አብሳሪ ከመሆኗም ባሻገር የጥሩ ዜጋ መፈጠሪያ፤ መሰሪያና ፍትህ የሚገኘባት ሰፍራም ናት፡፡ ሥራዋ ቀጣይነት እንድኖረው በክርስቶስ ፍቅር ውስጥ መኖር ነው፡፡
1. የእግዚአብሔርን ቃል ማስተማር ወይም መስበክ፡-
በማንኛውም ባህል ውስጥ ብንገኝ ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ ማር 16፡15 በማኅበራዊና ባህላዊ ጉዳዮች ላይ የሚኖረን ተሳትፎ በቅድስና የእግዚአብሔር ቃል መሠረት ያደረገ መሆን አለበት፡፡ለባልንጀሮቻችን ለባለሥልጣኖች ማድረግ የሚገባን ኃላፍነት ከቃሉ ያለፈ መሆን የለበትም ሮሜ 13፡1 ባልንጀራህን (ጎራበትህን) እንደ ራስ ውደድ የሚለውን የጌታ ትዕዛዝ ማክበር መስበክ አለብን፡፡ ማር 11፡28፡30
2. በእግዚአብሔር ፊት መፀለይ፡-
ፀሎት ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት የሚያደርግበት ቋንቋ ነው፡፡ ቤተክርስትያን ስላለችበት ኅብረተሰብም ሆነ ስለ መንግሥት ተግታ የመፀለይ ምዕመናኗም በግልም ሆነ በኅብረት ስለመንግሥታቸውና ስለአገራቸው እንዲፀልዩ ማደርግና ማነሳሳት አለባት፡፡ 1ጢሞ 2፡1-2 በምድር ላይ በማንኛውም ጊዜ እና ሥፍራ የምሥራቹን ወይም የሰላምን ወንጌልን የመስበክ ኃላፊነት አለብን፡፡
3. ሌሎችን ማስታረቅ
አምላካችን እግዚአብሔር የሰላም አምላክ ነዉ። ሰላምን ለማምጣት የሚጥሩ አስታራቂዎች የአምላካቸዉ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉ። የአማኞችም ዋነኛዉ ጥሪና ተልእኮም ይሄዉ ነዉ። እኛ የተጣሉትን ለማስታረቅ የተጠራን የማስታረቅንም አገልግሎት እንዲናገለግል የተጠራን ሰዎች ነን፡፡ እግዚአብሔር ዓለምን ከራሱ ጋር ካስታረቀ በኋላ ለእኛም የማስታረቅን አገልግሎት ሰጥቶናል፡፡ ‹‹ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።›› (2ቆሮ 5፡18-19)
ስለዚህ የዛሬዪቱም ቤተክርስቲያን ሌላ ተልዕኮ ሊኖራት አይገባም፡፡ አገልግሎቷም ኑሮዋም አንድና አንድ የማስታረቅ አገልግሎት ነው፡፡ የሰላም አለቃ የሚያድርባት፤ እርሱ ራሱ በደሙ የዋጃትና የመሰረታት ቤተክርስቲያን ባለችበት ሁሉ ሰላም ሊሆን ይገባል፡፡ ሌላው ደግሞ በምድር እንደመሆኗ መጠን የሰላም ችግር ባለበት ሁሉ ቤተክርስቲያን አስታራቂ ሆና መገኘት መቻል ይኖርባታል፡፡
የዛሬዪቷ ቤትክርስቲያን ሰላም በጠፋበትና ጸብ ባለበት እሳት ቆስቋሽና ቤንዝን አቀባይ ሆና መታየቷ በጣም የሚያሳፍርና የሚያም በሌሎች ዘንድ ምስክርነታችንን ያጠለሸ ጉዳይ ሲሆን ስለዚህ ነገር ሁሉም ሰዎች ከሚምር ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ዘንድ ምህረትን በፊቱ ወድቀን እንዲንጠይቅ የሚያስገድደን ጉዳይ ነው፡፡
የሰላም እንቅፋቶች
የሰላም እንቅፋቶች በምድር ላይ ብዙ ናቸው፡፡ ይህም የሰላም መደፍረስ በሰይጣን ጠንሳሽነት በኤደን ገነት አዳም ‹‹ከእኔ ጋር እንዲትሆን የሰጠኼኝ ሴት…›› (ዘፍ 3፡12) በማለት ሀላፊነት የጎደለው ሌላውን ጥፋተኛ በማድረግ ስሜት የተገኘ ግኝት ሲሆን ዛሬም የሰላም እንቅፋቶች ራሳችንን ባለማየትና ጥፋተኝነትን በሌሎች ላይ በማላከክ ሰላምን ለማምጣት የሚደረግ ጥረቶች ተልቁ የሰላም እንቅፋቶች ናቸው፡፡
1. ትዕብተኝነት (እኔነት)
ለኤፍሬም ሰካሮች ትዕቢት አክሊል፥ በወይን ጠጅ ለተሸነፉ በወፍራም ሸለቆአቸው ራስ ላይ ላለችም ለረገፈች ለክብሩ ጌጥ አበባ ወዮ! እነሆ፥ በጌታ ዘንድ ኃያል ብርቱ የሆነ አለ። እንደ በረዶ ወጨፎ፥ እንደሚያጠፋም ዐውሎ ነፋስ፥ እንደሚያጥለቀልቅም እንደ ታላቅ ውኃ ፈሳሽ በጠነከረ እጅ ወደ ምድር ይጥላል። የኤፍሬም ሰካሮች ትዕቢት አክሊል በእግር ይረገጣል፤…›› (ኢሳ 201-4)
ትዕቢት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከ60 በላይ በተለያዩ ጉዳዮች በቀጥታ ተጽፎ እናገኛለን፡፡ ትእቢተኝነት ከእኔነት ምንጭ ክፉና አጥፊ ባህርይ ነዉ። ‹‹… ይህች እኔ በጕልበቴ ብርታት ለግርማዬ ክብር የመንግሥት መኖሪያ እንድትሆን ያሠራኋት ታላቂቱ ባቢሎን አይደለችምን?›› (ዳን 4፡30) ትዕቢት እኔ አዉቃለሁ፣ ከእኔ በቀርና በላይ የለም በማለት ራሱን በመቆለል ይጀምራል። ትዕቢት የውድቀት ታላቅ ወንድሟ ነው፡፡ ‹‹ትዕቢት ጥፋትን፤ ኩሩ መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል፡፡›› (ምሳ 16፡18) እንደ ናቡከደነጾር ‹‹ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማነው›› (ዳን 3፡15) ማለትን ይወዳል፡፡ በትእቢተኛ አይን ፊት ሌላዉ ሰው ሁሉ ለምንም ነገር ብቁ አይደለም። ሌላው ቢኖር የማይጠቅም፣ ቢሞት የማይጎዳ ነዉ። ስለዚህም በትእቢት የተወጠረ ነዉ። ትእቢተኛ በዘሩ፣ በእዉቀቱ፣
በመልኩ፣ በኢኮኖሚው ይታበያል። እግዚአብሔር ግን ይቃወማቸዋል። ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ደግሞ ይደቃሉ።
ትዕቢት የሚመነጨው ከእውቀት ማነስ ነው፡፡ ‹‹በትዕቢት ተነፍቶአል አንዳችም አያውቅም፥ ነገር ግን ምርመራን በቃልም መዋጋትን እንደ በሽተኛ ይናፍቃል፤ ከእነዚህም ቅንዓትና ክርክር ስድብም ክፉ አሳብም እርስ በርስ መናደድም ይወጣሉ፥ አእምሮአቸውም በጠፋባቸው እውነትንም በተቀሙ፥ እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ (መንፈሳዊው ነገር ትርፍ ማግኛ አ.መ.ት) የሚሆን በመሰላቸው ሰዎች ይገኛሉ። እንደነዚህ ካሉት ራቅ። (1ጢሞ 6፡4-5) የትዕቢት ጉዞውም ወደ ሞት፤ ወደ ውድቀትና ውርደት ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹ትዕቢት ከመጣች ውርደት ትመጣለች፤ …፡፡›› (ምሳ 11፡2) በማለት ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ትዕቢተኞችን ሳይቀጣ፤ ትዕቢታቸውንም ሳያዋርድ አይተውም፡፡ ‹‹… የትዕቢተኞችንም ኩራት አዋርዳለሁ፡፡›› (ኢሳ 13፡11)
2. ቡድንተኝነት
ቡድንተኝነት የእኔነት ታላቅ ወንድም ሲሆን አድማሱንና ድንበሩን ሰፋ አድርጎ በሰፈር፣ በመንደር፣ በቀበሌ፣ እንዲሁም በወረዳና በዞን በድን በማደራጀት የሚደረግ የእኛ እንበልጣል፤ ለእኛ ይገባናል ባይነት የሚፈጠር የአስተሳሰብ ድክመት የወለደው አስተሳሰብ ነው፡፡ ቡድንተኝነት አንድ የተወሰኑ ግለሰቦች በተለይም ቀለም ቀመስ የሆኑ ግለሰቦች በቡድን በአንድ ጽንፍ ይዘው ለራሳቸው ጥቅም ለሌላው ማህበረሰብ/ህብረተሰብ ግድ የለሽና ደንታ ቢስ በመሆን ሁሉን ለራስ ብቻ ሲያስቡ ቡድንተኝነት ይወለዳል፡፡
3. ብሔርተኝነት/ጎሰኝነት
ብሔርተኝነት በአጭሩ በብሔር ላይ የተመሠረተ መድሎ ወይም ጭፍን ጥላቻ ማለት ነው፡፡ ብሔርተኝነት አንድን ሰው/ብሔር ከሌላው ሰው/ብሔር የመለየት ተግባር ነው፡፡ ብሔርተኝነት አንዱ የማህበረሰብ ወገን ራሱን ከሌሎች ማህበረሰብ የበላይነትን የልዩነት አስተሳሰብ በመያዝ የእኔ ማህበረሰብ ይበልጣል ብሎ በማሰብ የሌላኛውን ማህበረሰብ ብሔር፣ ጎሳ፣ ቋንቋ፣ አመለካከት፣ አኗኗርና የሕይወት ሥርዓት በመናቅ፣ በማጣጣል እንዲሁም አንቋሾና በተቃርኖ በመረዳት እስከ ማጥቃትና ማጥፋት የሚያደርስ አንዱ የበላይ አንዱ ደግሞ የበታች አድርጎ የመመልከት ችግር ነው፡፡ ይህንን አመለካከት ሰፋ አድርገን ስንመለከተው የብሔር፣ የጎሳ እና የቋንቋ ልዩነቶችን በመጠቀም የራሱ ብሔር ወይም ጎሣ ያልሆነውን የማህበረሰብ ክፍል ዝቅ አድርገው በማስቀመጥ ከመሠረታዊ ነገሮች ተጠቃሚ እንዳይሆኑና የማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚዎች እንዳይሆኑ መንፈግ ነው፡፡ በብሔርተኛ መሪ ሀገር ስትመራ ቁልፍ የአመራር ደረጃዎች ላይ የራሴ የሚለውን ብሔር በማስቀመጥ የሀገሪቱ ተቀዳሚ ሀብት ለራሱ ብሔር በመመደብ ለሌሎቹ ደግሞ የሚጋጩበትን አብላይ ሐሳብ በመስጠት ያጋጫቸዋል፡፡
ሰው ብሔርተኝነትን ይማራል እንጂ አብሮ አይወለድም፡፡ ሰው መሆን ከብሔርና ከጎሳ ይቅድማል፡፡ የሰው ልጅ ስወለድ ዘር እንጂ ብሔር የለውም፡፡ ሰው የሰው ዘር ሆኖ ነው የሚወለደው፡፡ ሰው ስወለድ ጎሳ፣ ብሔር፣ ቋንቋም አልነበረንም፡፡ ስለዚህ ሰው ብሔርተኝነትን ይማራል እንጂ አብሮት አልተወለደም፡፡ በብሔርተኝነት ተግባር ከሁሉም በላይ ብሔርተኝነትን ለማስፋፋት ሚና የሚጫወቱት በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ባለስልጣናት ብሔርተኝነትን በማስተማርና በመስበክ የሀገረውን ሕዝብ በመከፋፈል የራሳቸውን ተጠቃሚነት ያራዝማል፡፡ በእንደነዚህ ባለው የብሔርተኝነት አመለካከቶች የሀብት ተጠቃሚነት የተነፈጋቸው ሰዎች መብታቸውን ለማስጠበቅ በሚል እሳቤ በሚደረግ ግብግብ የሰላም እጦት ይከሰታል፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ
እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ ይወዳል፡፡ (የሐ 3፡16) እግዚአብሔር በሰዎች መካከል አያዳላም፡፡ (ዘዳ 10፡17) እግዚአብሔር የሁሉም ጌታ ነው፡፡ (ሐዋ 10፡36፤ ሮሜ 2፡9-11፤ ኤፌ 6፡9) እግዚአብሔር አያዳላም፡፡ የእግዚአብሔር ዘር የሆነ ዘርም የለም፡፡ ሁሉም የእግዚአብሔር ነው፡፡ ሁሉም ደግሞ ከእግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔር ያለ አድሎ ሁሉንም ዘር በታላቅ ፍቅሩ ወዶአል፡፡ መፍትሔው ምንድነው
3.1. መቻቻል
‹‹ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ለመኖር የሚቻላችሁን ሁሉ አድርጉ፤ …፡፡›› (ዕብ 12፡14 አ.መ.ት)
መቻቻል አትንካኝ አልነካህም፤ አትድረስብኝ አልደርስብህም ማለት አይደልም፡፡ መቻቻል ለሰዎች ባለን አክብሮት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ መቻቻል ሰላምን የሚናሰፍንበት የሞራል እሴት ሲሆን ለልዩነቶችቻችን እውቅና መስጠት ነው፡፡ ለፍትሃዊ፣ ለሚዛናዊና ለሰላማዊ ማህበረሰብ በጣም ወሳኝና አስፈላጊ ከሆኑት የሞራል እሴቶች አንዱ መቻቻል ነው፡፡ መቻቻል ሰዎችን በማንነታቸው መቀበል፣ ይቅር ባይ መሆንና ሰላማዊ ግንኙነት ማድረግ ነው፡፡ መቻቻል በማህበረሰብ ውስጥ የሕይወት መሠረት ነው፡፡ ያለመቻቻል በማህበራዊ ሕይወትም ውስጥም ሆነ በተፈጥሮ ጋርም መኖር አይቻልም፡፡ መቻቻል ከትዕግስት የሚመነጭ ሲሆን ልዩ የሆነ ለሰው ልጆች የተቸሬ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው፡፡ ሰዎችና እንስሳት በኖህ መርከብ ተቻችለው ባይገቡና ገብተውም ተቻችለው ባይኖሩ ኖሮ ዛሬ ምንም ዘር ባልቀረልን ነበር፡፡ ስለዚህም ነው መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።›› (ሮሜ 12፡18) የሚለን፡፡ መቻቻል በክርስቲና ሕይወት ውስጥ ዋነኛውንና ቁልፍ ቦታ ይይዛል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎቱን በሚያከናውንበት ዘመን በአይሁዳዊያንና ሳምራዊያን መካከል ያለመቻቻል ነበር፡፡ (ዮሐ 4፡9) በአይሁድ የሐይማኖት መሪዎችና በሕዝቡ መካከልም እንዲሁ ነበር፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከሁሉም ጋር በፍቅር ይተባበር ነበር፡፡ ሁሉንም ያገለግላቸው ነበር፡፡ ለአየሁዳዊም፣ ለሳምራዊውም እኩል እይታ ነበረው፡፡
3.2. መከባበር
‹‹በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤ …፡፡›› (ሮሜ 12፡10) ሁሉን እክብሩ፤ ወንድሞችን ውደዱ፤ እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ንጉስን አክብሩ፡፡ (1ጴጥ 2፡17)
መከባበር የሞራል እሴት ነው፡፡ መከባበር ሰዎች በማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ በመደጋገፍ እና አብሮ ለመኖር አሰፈላጊ ከሆኑት የሞራል እሴቶች አንዱ ነው፡፡ መከባበር ከሁሉም ማህበረሰብ ጋር በሁሉም መስማማት ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን አንዱ ማህበረሰብ ወይም ግለሰብ በሌላው ላይ ጉዳት የማያደርስ ወይም ተጽዕኖ የማያሳድር ከሆነ የዚያን ማህበረሰብ ወይም ግለሰብ በኣኗኗሩ እና በውሳኔዎች ምክንያት አለማድላት ወይም አለማስቀየም ነው፡፡ መከባበር ማለት አንድ ዓይነት ፍላጎት ከሌላቸው ሰዎች ጋር ተቻችሎ አብሮ መኖር ማለት ነው፡፡
መከባበር የዜግነት እሴት ነው፡፡ ለሀሳቦች ብዙሃነትና ለአስተያየቶች ፍትሃዊና ሚዛናዊ ክብር መስጠት አብሮ ለመኖር ብቸኛውና ዋነኛው እሴት መከባበር ነው፡፡ ከሌሎች ጋር ጤናማ ግንኙነት እንዲኖረን አስፈላጊ ከሆኑት ሕጎች አንዱ መከባበር ነው፡፡ መከባበር ኃይማኖታዊ እሴት ነው፡፡ ‹‹አባትህንና እናትህን አክብር፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው።›› (ማቴ 19፡19) እግዚአብሔር ወላጆቻችንና ባለንጀሮቻችንን እንዲናከብር አዞናል፡፡ ‹‹ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ግብር ለሚገባው ግብርን፥ ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን፥ መፈራት ለሚገባው መፈራትን፥ ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ።›› (ሮሜ 13፡7)
ሌላው ደግሞ አንዱ የአንዱን የእምነት ቀኖና ሳይንቅና ሳያንቋሺሽ ማክበር ተደጋግፎ አብሮ ለመኖር ከሚያስፈልጉት መርሆች አንዱ ነው፡፡ ‹‹በእምነቱ ደካማ የሆነውን ሰው አከራካሪ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በአቋሙ ሳትፈርዱበት ተቀበሉት፡፡›› (ሮሜ 14፡1 አ.መ.ተ) አይሁድም ሆኑ የግሪክ ሰዎች ሁሉንም በክርስቶስ ፍቅር ሊንወዳቸው ያስፈልጋል፡፡ እኛም በክርስቶስ ኢየሱስ ያመነን ክርስቲያኖች ከእርሱም የተማረነው ፍቅርን ነው፡፡ ፍቅር ደግሞ አይመካም፡፡ አይታበይም፡፡ በደልን አይቆጥርም፡፡ ፍቅር ይታገሳል፡፡ ፍቅር ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፤ በሁሉም ይጸናል፡፡ 1ቆሮ 13፡1-7
ሰላም እንዲሆን የእኛ ድርሻ ምንድ ነው
አለመግባባቶችን ማስወገድ
የአመለካከትና የድርጊት ምላሾችን በተመለከተ ጠንቃቃና አስተዋይ መሆን
ሰላም ’’PEACE’’ ለማምጣት የእኛ ድርሻ
P – Pray/መጸለይ:- በምድር ሰላም ለሰው ልጆች እረፍት እንዲሆን እግዚአብሔርን መጠየቅ
E – Explore/መፈለግ፡- ሁሉም ወገኖች ያላቸውን አመለካከት ሰላም እንድሆን መፈለግ
A – Approach/መቅረብ:- በክርስትያናዊ አመለካከት አንዱ ከሌላው ጋር በመልካም ግንኙነት መቀራረብ
C – Collaboration/መተባበር:- በጋራ በመተባበር በፍቅር በሰላም እንድኖሩ ማድረግ
E – Expel/መተው (ትቶ መውጣት):- ከሌሎች ጋር ሰላምን በመፍጠር ያለፈውን በመተው በአዲስ ልብና አመለካከት እንዲኖር ማድረግ ማቴ 5፡24
የሰላም ዓይነትና ባህርያት
1. ውስጣዊ ሰላም ፡-
የውስጣዊ ሰላም ሊገኝ የሚችለው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፡፡ ሰዎች የሰላም ባለበት እራሱ ሰላም ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር ባላቸዉ ጥብቅ ግንኙነት ነው። የዚህ ዓይነት ሠላም ባለቤቱ እግዚአብሔር ነው። ዉስጣዊ ሰላም የሰላሙ ባለቤትና ምንጭ በሆነዉ በእግዚአብሔር ላይ በመታመንና በመደገፍ የሚገኝ ነው። (ኢሳ 26:3)
ስለዚህ ውስጣዊ ሰላም የሚገኘዉም ከእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ነዉ። ዉስጣዊ ሰላምን ዉጫዊ አካል የሆኑ፣ ገንዘብ፣ ሀብት፣ እዉቀት፣ ዝነኛነት፣ የፖለቲካ ድርድሮች የመሳሰሉት ሊሰጡን አይችሉም። ’’በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።’’ (ዮሐ .ወ 16:33)
ውስጣዊ ሰላም ለማግኘት በመጀመርያ መሠረታዊ ደረጃ
1.1. ከራስ ጋር መታረቅ
ሰው ከራሱ ጋር መታረቅ መቻል አለበት፡፡ ሰው ከራሱ ጋር ከታረቀ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ አይሳነውም፡፡ ሰው ደስተኛ ሕይወት ለመኖርና ሰላምን ለማግኘት ከእግዚአብሔር ጋር መስማማት ይኖርበታል፡፡ እግዚአብሔርም መሐሪ ስለሆነ ሰው ጥፋተኝነት ተስምቶት ላጠፋው ጥፋት ሀላፊነት ወስዶ በአግዚአብሔር ፊት ስቀርብ እግዚአብሔር ይቅር ይለዋል፡፡
1.2. ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ
ሰው ከራሱ ጋርና ከእግዚአብሔር ጋር ከታረቀ ውስጣዊ ሰላምን ያገኛል፡፡ መዝ ዳዊ 32፡1-2 ‹‹መተላለፉ ይቅር የተባለለት ኃጢአቱ የተሸፈነለት …. ሰው እንዴት ደስተኛ ነው›› ሰው ከራሱ ጋር ከታረቀ፤ ከእግዚአብሔርም ጋር ከታረቅ፤ ከጎራቤት ወይም ከባልነጀራ ጋር እንዲሁም ከኅብረተሰብ ጋር መታረቅ ይችላል፡፡ ‹‹እኛም የበደሉንን ሰዎች ይቅር እንደ ምንል በደላችንን ይቅር›› በለን ማለት አለበት፡፡
1.3. ከጎረበት/ከባልንጀራ ጋር መታረቅ
ውስጣዊ ሰላም ከራስ፣ ከእግዚአብሔርና ከጎረቤቶች ጋር የሚደረግ እርቅ ብቻ ሳይሆን ሰው ከተፈጥሮ ጋር የሚደረግ ዕርቅ ነው፡፡ ሰው ከእነዚህ ሁሉ ጋር ተሳስቦ፣ ተደጋግፎና ተጋምዶ መኖር ስችል ውስጣዊ ሰላም ይኖረዋል፡፡ እንግዲህ ሰላም በውስጣችን እንድኖር እምነትና በጎ ኅሊና መያዝ፤ (1ጢሞ 1፡8-20 ፤4፡16) እውነትን መውደድና መከተል፤ (ምሳ 8፡13 2ተሰ 2፡9-12) ይኖርባናል፡፡
ውስጣዊ ሰላም ከዉስጥ ወደ ዉጪ የሚፈስ/የሚገለጥ ነው። ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም። (ዮሐ 14:27) እግዚአብሔር አእምሮን የሚያልፍ ሰላም እንደሚሰጠን መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡ (ፊልጵ 4:6) ውስጣዊ ሰላም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ከውስጥ የሚፈልቅ አዕምሮን የሚያልፍ ሰላም ነው። የእግዚአብሔር ሰላም በአእምሮ ቀመር ላይ የተመሠረተ አይደለም።
2. ውጫዊ ሰላም ፡-
’’ከሌሎች ጋር እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሱ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ፡፡’’ ኤፌ 4፡3
ሰው ውስጣዊ ሰላም ከሌለው ውጫዊ ሰላም ሊኖረው አይችልም፡፡ ሰው ከራሱ እና ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ካልሆነ ከባልንጀራው ጋር ሰላም መሆን አይችልም፡፡ ሰው ከባለንጀራው ጋር ሰላም ሊሆን ካልቻለ ውጫዊ ሰላም ሊኖር አይችልም፡፡ ሰው ከባልንጀራው ጋር በሰላምና በፍቅር መኖር ስችል ውጫው ሰላም የተጠበቀ ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ባልንጀራን እንደ ራስ ውደድ›› ይላል፡፡ (ማቴ 22፡39) በመጽሕፍ ቅዱስ ያለው የእግዚአብሔር ሕግ ለሀገር ሕግ ሁሉ መሠረት ነው፡፡ የሀገራት መንግሥታት የሚያወጡት ሕግ ቢቻላቸው በዜጎቻቸው መካከል መተሳሰብ፣ እኩልነትና መከባበር እንዲኖር ሚያደርግ ይሆናል፡፡ ይህ ደግሞ ሊመጣ የሚችለው ሰው ባልንጀራውን ስወድ ነው፡፡ ሰላም ደግሞ ከመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ነው፡፡ ሰላምን የሚከለክል ሕግ የለም፡፡ ‹‹የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም።›› (ገላ 5፡23) ቤተክርሰትያንን ሰላሟን ከሚያደፈርሱ ተግዳሮቶች መጠበቅ
ቤተክርስቲያንን መጠበቅ ስንል ህጻውን መጠበቅ ማለት አይደለም፡፡ ቤተክርስቲያንን መጠበቅ ስንል በክርስቶስ አምነው እርሱን እያመለኩና እያገለገሉ ያሉትን የክርስቲያኖችን/የአማኞችን ኅብረት ከክፉ ተግዳሮት መከለል/መጠበቅ ማለት ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ሰላሟ እንዳይደፈርስ ከውጫዊ ተግዳሮትና ከውስጣዊ ተግዳሮት ለመከልከልና የሕዝቡን መንፈሳዊ ሕይወት ለማሳደግ ከእግዚአብሔር ጋር በመተባበር ጠንክሮ መሥራት ይኖርብናል፡፡ (ኤፌ 4፡14-15) በሕዝባችን መካከል ወሬና ሐሰትን በመበተን መለያየትን ለማምጣት የምሯሯጡትን የሰይጣን ተላላኪዎችን በቤተክርስቲያን ፊት ለፊት አጋልጦ በመገሰጽ፣ በመንገርና እውነተኛውን ቃል በማስተማር መለወጥ ሥፍራ እንዳያገኙ መድረግ አለበት፡፡ (ገላ 2፡4-5)
Start a discussion with Talargachew Tamirat Biru
Talk pages are where people discuss how to make content on ውክፔዲያ the best that it can be. Start a new discussion to connect and collaborate with Talargachew Tamirat Biru. What you say here will be public for others to see.