አባል ውይይት:Tatekgetye
ርዕስ ጨምርበማሽላው መሀል እየተጎማለልሽ ለልቤ መሸፈት ምክንያትም የሆንሽ አንቺ ያገሬ ልጅ ከቶ እንደምን ከረምሽ እኔ እንደምወድሽ አንቺም ታውቂዋለሽ፡ እኔ እንደወደድኩሽ አንችም ወደጅኝ ኑሮ ለመመስረት ምርጫሽ አድርጊኝ ማሽላ አኮታኮት እያስተማርሽኝ ለማጅ ስለሆንኩኝ ቀስ ብለሽ ያዥኝ ዳገቱ በበዛዉ በመጅት ወርደሽ ወደት እንገናኝ እኔ ሞትኩልሽ አካ ገብርኤል ሲሉኝ በስርጡ ወረድኩኝ እኔ አንቺን ለማግኘት እንዳይሆን ደከምኩኝ አንቺ ግን ያለሽው ከማሽላው ውስጥ ስታንጎራጉሪ ቃሉሲመስጥ እንኳን ዳገትና ያስሮጣል በስርጥ ከማሽላው መሀል የዘራሽው ጥንቅሽ እንድትወደጂ አርጎ የሰራሽ ምን ጥፋት ብትሰሪ እኔ እንደት ልጥላሽ በኸራ ሄደሻል ማክሰኞ ገበያ በዚህ አጋጣሚ እስኪ እንወያያ ከሰፈሬ መጥተሽ ካደኩበት ቦታ ለምን ወደ ኀላ ለምንስ ላመንታ እንሄዳለን ሚዳ ከሰፊዉ ከተማ እንወጣዋለን ፍቅርን ስንጠማ ነይ መላ ነይ መላ አቅርቤ ለብቻ ላልበላ እውነት ነው ታስፈልጊኛለሽ በጎደለው ቦታ አንቺ ታሟሊአለሽ ውብ እኮነሽ ደግሞ፡ያገሬ ልጅ የማር ሰፈፍ የሌለው እጭ ነይ ነይ ያገሬ ልጅ ነይ ፍቅራችን ይበልፅግ እኛ እንዳንለያይ እኛ ከጀመርነው፡ይረዳናል ከላይ፡፡ መሽቶም አይነጋልኝ፡አይንሽንም ካላይ፡፡ ትመጫለሽ ብዬ ፡አጥር ስር ቆሜአለሁ፡፡ ያን መንታ መንገዱን፡ እጠባበቃለሁ፡፡ የወሰደ መንገድ ፡እኔ ወቅሻለሁ፡፡ ብቻ አንቺ ከመጣሽ፡ እጠብቅሻለሁ፡፡ መሬ ላይ ሄድሽ አሉ ለትምህርት ብለሽ፡፡ ለፈለገሽ ልቤ፡ሀዘንንም ትተሽ፡፡ ኦፍና አማኑኤልን በቁም ተሳልመሽ፡፡ ሰው ሆነሽ ተፈጥረሽ፡በሰው ጨክነሽ፡፡ ወደ ኀላ ሳታይ ፡በርቃቶ ደረሽ፡፡ ልትመንኒ ነወይ፡ደብረ ሊባኖስ፡፡ ለኔ ኃጺአተኛው፡ልትሆኝ ነብስ፡፡ ፍቅርን ጥለሽ ሄደሽ፡ጸሎትም አይደርስ፡፡ በጣም በዝቶብሻል፡የዓለም መንፈስ፡፡ ስለ ፍቅር እንጂ፡ካንጀትስ ማልቀስ፡፡ ክርስቶስ ከሰማይ፡እምድር እስቲደርስ፡፡ ፍቅር ነው የሳበው፡ጥል ሊደመስስ፡፡ ፍቅርን በመተው፡ከተገኘ ነብስ፡፡ አስከትይኝና፡እኔም ልመልኩስ፡፡ ወታደር አይደለሁ፡አልችልበት ተኩስ፡፡ ታዲያ በምንድን ነው ፡ለሰው እምደርስ፡፡ ማሽላውን ትተሽ ፡የኮተኮትሽውን፡፡ ከየት ልታመጪው፡ገዳምስ ዳቤውን፡፡ እባክሽ ቅሪና፡መግቢ ሌላውን፡፡ በዚህ ከኮነነኝ፡እኔ ልጠዬቅ፡፡ አንጀቴ አልችል አለ ፡ካንቺ ለመራቅ፡፡ ታጠቅ ጌትዬ ነኝ ከ አዲስ አበባ
Start a discussion with Tatekgetye
Talk pages are where people discuss how to make content on ውክፔዲያ the best that it can be. Start a new discussion to connect and collaborate with Tatekgetye. What you say here will be public for others to see.