Jump to content

አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት

ከውክፔዲያ

አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅትአዲስ አበባኢትዮጵያ በመንግስት ባለቤትነት የሚተዳደር ከከተማ አውቶቡስ የህዝብ ማመላለሻ አገልግሎት ሰጭ ድርጅት ነው።

አንበሶች በድርጅቱ ምስረታ ወቅት ለነበረው ንጉሣዊ ሥርዓት ትልቅ ግምት ስለነበራቸው ብዙ ተቋማት በስማቸው ይሰየሙ ነበር። አንበሳ ከተመሰረተ በኋላ ብዙም ሳይቆይ በአቶ ተፈሪ ሻሞ ነበር ስያሜውን ያገኘው። ይሁንና በ2015 ከ80 ዓመታት አገልግሎት በኋላ ድርጅቱ ስያሜውን በመተው "የከተማ አውቶቡስ" ተብሏል። ሆኖም ነባር ተሽከርካሪዎች በውጫዊ ገጽታቸው ላይ አሁንም ስሙንና አርማውን አልቀየሩም።

አንበሳ ሥራ የጀመረው ጣሊያኖች ኢትዮጵያን ከወረሩ በኋላ የተዉትን የጭነት መኪናዎች በሞደፊክ በመለወጥ ነው። እስከ 1948 ዓ.ም ድረስ መደበኛ ባልሆነ መንገድ ሲሰራ ቆይቶ የአንበሳ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት በሚል በንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ በአንዳንድ የመንግሥት ኩባንያዎች እና በንጉሣዊ ቤተሰብ አባላት ባለቤትነት እንደ አክሲዮን ማኅበር በይፋ ተጀመረ። 40 ጣሊያናዊ አሽከርካሪዎችና መካኒኮች ከ80 ኢትዮጵያውያን ሰልጣኞች ጋር ነበሩት።

የመጀመሪያው የአንበሳ አውቶቡሶች ቀለም ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት በመነሳት አረንጓዴና ቢጫ የነበረ ሲሆን ሁለት መስመሮች ብቻ ነበሩት፡- እነዚህም :-

  • መስመር 2: ፒያሳ እስከ ገነት ሆቴል
  • መስመር 4: ሲኒማ ኢትዮጵያ እስከ ካዛንቺስ

ነበሩ።

በድርጅቱ ለረጅም ጊዜ ሲያገለግል የነበረው አንበሳ ሲዘልል የሚያሳየው አርማ የተነደፈው በጣሊያናዊ አርቲስት ነው።

በድጋሚ የቀለማት ማሻሻያ፣ አንበሳ ቀለሙን አሁን ወዳለው ቢጫና ቀይ ለውጧል፤ ምንም እንኳን አንዳንዶች ይህ የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ መለያን መሠረት ያደረገ ነው ብለው ቢከራከሩም ቀለሙ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የታችኛው ሁለት ቀለማት ላይ የተመሠረተ ነው። ።

በ1974 ዓ.ም የደርግ ወታደራዊ መንግሥት የአክሲዮን ማኅበሩን በመበተን ድርጅቱን ወደ መንግሥት ይዞታነት አዛወረው።

በ1991 ዓ.ም ከደርግ ውድቀት በኋላ ኢህአዴግ እንደ ህዝብ ድርጅት በድጋሚ አቋቋመው።

በኢህአዴግ አመራር ስር አንበሳ በአገር ውስጥ በብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (METEC) የተገጣጠሙ በርካታ አውቶቡሶችን ገዝቷል። ከእነዚህ በአገር ውስጥ ከተገጣጠሙትና የመገጣጠሚያ ፋብሪካው ከሚገኝበት ከተማ ስም በመነሳት "ቢሾፍቱ አውቶቡሶች" በመባል ከሚታወቁት ከ500 በላይ የሚሆኑትን አውቶብሶች ይጨምራል።ምንም እንኳን አንበሳ የሚያገለግለው በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ልዩ ዞኖች ብቻ ቢሆንም ከእነዚህ አውቶቡሶች ውስጥ ስምንቱ ጂማ ውስጥ ይገኛሉ። በአሁኑ ጊዜ በድርጅቱ ሥር ወደ 1000 የሚጠጉ የከተማ አውቶቡሶች አሉ። ከእነዚህ ውስጥ ወደ 40 በመቶ የሚሆኑት በቴክኒክ ችግሮች ምክንያት ከአገልግሎት ውጪ ነበሩ።

በ2015 አ.ም የአንበሳ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በአንፃራዊነት አዲስና አነስተኛ ከሆነው ሌላኛው የመንግሥት የከተማ አውቶቡስ ድርጅት ፣ ከሸገር አውቶቡስ ጋር ተዋሀደ። የተዋሀደው ድርጅትም "ከተማ አውቶቡስ" በመባል ተጠራ፤ ይህ የድርጅቱን ታሪካዊነት የሚሽር እንቅስቃሴ ነው በሚል ከፍተኛ ትችት አስነስቷል። ውህደቱ የአውቶቡሶችን ቀለም ወደ ሙሉ አረንጓዴ መቀየርን ያካተተ ቢሆንም ተግባራዊ አልሆነም፤ ሆኖም ከሁለቱም ኦፕሬተሮች የተገኙ አውቶቡሶች ከ2017 ዓ.ም. ጀምሮ ከመዋሃዳቸው በፊት የነበረውን የመጀመሪያውን ቀለምና ስም በውጫዊ አካላቸው ላይ ይዘዋል። ውህደቱን ተከትሎ ከድርጅቱ ወደ 400 የሚጠጉ ሠራተኞችን በዘፈቀደ ከሥራ መሰናበታቸው ውዝግብ አስነስቷል።

ተሽከርካሪዎች

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ዳፍ 2105 የአንበሳ አውቶብስ ተሽከርካሪ
  • ፊያት ትሬንታ-ኳትሮ የጭነት መኪናዎች
  • ቢአማክስ የመርሴዲስ አውቶቡሶች፣
  • ታታ አውቶቡሶች
  • ኢካሩስ አውቶቡሶች ፡ ህብረተሰባዊነት በሚያቀነቅኑ ሀገራት ውስጥ በስፋት ይገኝ የነበረ የሶቭየት መኪና
  • ቮልቮ አውቶቡሶች
  • መርሴዲስ ጆንክሄር ፡ በማርቸዲስ ሻንሲ ላይ የተሰሩ የሆላንድአውቶብሶች
  • ዳፍ ቤርክሆፍ ጆንክሄር ፡ በዳፍ TB2105 ሻንሲ ላይ የተሰሩ
  • ሁዋንግሃይ ቢሾፍቱ ፡ በሁዋንሃይ ተመርተው ቢሾፍቱ ውስጥ የተገጣጠሙ


ድርጅቱ ታሪካዊ አውቶብሶችን ለቅርስነት የሚያስቀምጥበት አሰራር የለውም።





ዩቶንግ ZK6126HG አንበሳ አውቶብስ ስታዲየም ተርሚናል አካባቢ

ከ2012 ጀምሮ አብዛኛዎቹ ተሽከርካሪዎች ደረጃ አልባ፣ ባለ ፎቅ እና መካከለኛ ወለል ዲዛይን ያላቸው የዩቶንግ አውቶቡስ ሞዴሎች ናቸው። ከነዚህ አውቶቡሶች አብዛኞቹ በቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ የተገጣጠሙ ሲሆኑ የተወሰኑት ከቻይና የገቡ ናቸው።




ድርጅቱ በዋና ከተማዋና ዙሪያዋ በ172 መስመሮች ይሰራል። ከድርጅቱ ጋር የተዋሀደው ሸገር አውቶቡስ የአንበሳን መስመሮች በመከተል ቀድሞ የነበረውን የነበረውን መስመሮች ትቷል።

በተጨማሪም ይመልከቱ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
  • ትራንስፖርት በአዲስአበባ
  • ኮንትራት ታክሲ