አይሁድ ኢየሱስን ለምን ገደሉት
Appearance
ዮሃ10፡33-32 ኢየሱስ፦ ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው። አይሁድም፦ ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት። ኢየሱስ አይሁድ ይህን ሲሉት ለተረዱት አረዳድ እርማት አልሰጠም ላመቻመቸም ይቅርታም አልጠየቀም። ይልቁን በዚሁ አባባሉ በመቀጠሉ ምክንያት በርግጥም ገድለውታል።ከገደሉትም በኋላ የእግዚያብሄር ልጅ ከሆንክ እስቲ ከመስቀል ላይ ውረድ ብለው ዝተውበታል። ሌላው ቢቀር ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ እኔን ማን ትሉኛላችሁ ብሎ ደቀ መዛሙርቱን ለጠየቀው ጥያቄ የሃዋርያው ጴጥሮስ መልስ "አንተ ክርስቶስ የእግዚያብሄር ልጅ ነህ"ብሎ ሲለው አልገሰጸውም።አባባሉ ለራሱ እንደሚመጥነው አድርጎ ተቀብሎታል። ማቴ 16፡16 ይህንን የመሳሰሉትን ንግግሩን ጭምር ስንመለከት ኢየሱስ በአይሁድ ለመገደሉ በጣም በቂ ማስረጃ አለ። አይሁድ ኢየሱስን የገደሉት በበቂ ማስረጃ ያውም በራሱ አንደበት በወጣ ማስረጃ ነው። ኢየሱስን ሰቅለውታል ገድለውታልም በሶስተኛው ቀን ግን ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል