ኢዲን-ኢሉም

ከውክፔዲያ
የኢዲን-ኢሉም ሐውልት

ኢዲን-ኢሉም (ወይም ኢዲ-ኢሉም) በኡር መንግሥት ጊዜ በሹልጊ ዘመን የማሪ ሻካናካ ወይም ገዥ ነበረ። ይህ ከ1959 እስከ 1954 ዓክልበ. ግድም ድረስ ነበር።

በተለይ የሚታወቀው በሥነ ቅርስ ስለ አንድ ሐውልት ነው። ከጢሙ ጫፍ በቀር የሐውልቱ ራስ ጠፍቷል። በሐውልቱ የተቄረጹት ርጉም ቃላት እንዲህ ይላሉ፦ «ኢዲን-ኢሉም፣ የማሪ ሻካናካ፣ ይህን ሐውልቱን ለኢናና (አረመኔ ጣኦቷ) አስረክቧል። ማናቸውም ይህን ጽሑፍ የሚደምስስ፣ ኢናና ዘሩን ትደምስስ።»

የኢዲን-ኢሉም ልጅ ዚኑባ ስም ደሞ ከአንድ የሸክላ ማህተም ይታወቃል።

ቀዳሚው
አፒል-ኪን
ማሪ ሻካናካ
1959-1954 ዓክልበ.
ተከታይ
ኢሉም-ኢሻር