እምቡሊ
Appearance
እምቡሊ በአማራ ክልል በማቻከል ወረዳ የምትገኝ ታዳጊ ከተማ ናት።ከአዲስ አበባ በ 340 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። በሰሜን ደምበጫ በደቡብ አማኑኤል ያዋሱኗታል። አካባቢዋ በምንጭ የተጥለቀለቀ በመሆኑ ዉሀዋ ከሁሉም አካባቢ የተለየ ነዉ። በአካባቢዉ በቆሎ በብዛት ይበቅላል። አካባቢዉ በተደጋጋሚ የመሬት መሰንጠቅ እና መናድ ያጋጥመዋል። የወተት ምርትም የአካባቢዉ ማህበረሰብ መተዳደሪያ ነዉ።የህዝቧ ብዛት በዉል አይታዉቅም። ግምት ከ 5000 በላይ ይሆናል። በደኗ ግራር፣ዋርካ፣ሊጊጣ፣ዋንዛ የመሳሰሉት ይበቅላሉ።አንድ ት/ቤት አላት።