Jump to content

እንዳለጌታ ከበደ

ከውክፔዲያ

#የኢትዮጵያ_ደራስያን_ማህበር_ዋና_ፀሐፊ የሆነው ደራሲ Endalegeta Kebede / እንዳለጌታ ከበደ ለአንባቢያን ካደረሳቸው መፅሀፌት መሀከል:-

1. እምቢታ

2. ደርሶ መልስ

3. ዛጎል

4. የመኝታ ቤቶች ምስጢሮች

5. ኬር ሻዶ

6. ከጥቁር ሰማይ ሥር

7. በዓሉ ግርማ ሕይዎቱና ሥራዎቹ

8. ምሳሌ

9. ጽላሎት

10. መክሊት

11. ያልተቀበልናቸው

12. ማዕቀብ

13. ደቦ

14. ሲጥም

15. የካሳ ፈረሶች (ታሪካዊ ተውኔት)

መፃሕፍትን ለንባብ ያበቃ ሲሆን በሌሎች መድበሎችም ሥራዎቹ ታትመውለታል፡፡

እንዳለጌታ (ዶክተር) ዛጎል የመጽሐፍት ባንክ መስርቶ መጽሐፍትን ሰብስቦ ለማረሚያ ቤቶችና ትምህርት ቤቶች ማሰራጨት የሚታወቅበት ተግባሩ ነው።

"ልዩነቱ ይሄ [የመጽሐፍት ባንኩ] የተደራጀ የተቀናጀ ቋሚ ቢሮ፣ ቋሚ ሠራተኛ ያለው ወጪ የሚጠይቅ ጉልበት የሚጠይቅ መሆኑ ነው። .... ያነበቡ እንዴት እንደሚፈወሱ አይቻለሁ። ያነበቡ የሚያደርጉትን ያውቃሉ። የሚያደርጉትን ካወቁ ደግሞ ኃላፊነት ይሰማቸዋል። ኃላፊነት የሚሰማው ደግሞ ለራሱም ለአገሩም መድኃኒት ለመሆን እንጂ ችግር ውስጥ ለመክተት የሚተጋ አይሆንም " ሲል ለዛጎል የመጽሐፍት ባንክ መመስረት ምክንያት የሆነውን ጉዳይ ያስረዳል።

ደራሲ፣ ገጣሚ፣ የጨዋታ ፈላስፋ ፣ጋዜጠኛ የትያትር ባለሙያ ዶ/ር የሚሉት ሁሉ ከእርሱ ስም በፊት የሚመጡ ናቸው። የብርሀኑ ዘርይሁን ምርኮኛ የበዓሉ ዘገር ነቅናቂ የስብሐትን እሴት መስካሪ ከምንለው በላይ እኔ በሀገር መልካም ማዕረግ እንዳለጌታ ከበደ ሚለው ስም ይገዝፍብኛል።

መላኩ ዳንኤል (MelDan)