Jump to content

እውን ነብዩ መሀመድ ሀሰተኛ ናቸው?

ከውክፔዲያ

ቢስሚላህ አልሀምዱሊላህ

እውን ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ሀሰተኛ ነብይ ናቸው? ሀሰተኞች አላማቸው አለማዊ ጥቅም ማግኘት ነው ማለትም ለስልጣን፣ ለክብር፣ ለዝና፣ለገንዘብ፣ለሴት.... ብለው ነው ነብይ ሳይሆኑ ነብይ ነኝ ሚሉት። ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች አብዛኞቹ ሚያስቡት ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ነብይ ነኝ ሲሉ ሁሉም ሰው ባንዴ ነብይነታቸውን ተቀብሎ ያመናቸው እና የተከተላቸው አርገው ነው ሚያስቡት። ነገሩ ግን በተገላቢጦሽ ነው የሆነው።

ከነብይነታቸው በፊት ታማኙ ሙሀመድ በተባሉበት ምላስ አላህ ነብይ አድርጎ ልኮኛል ሲሉ

ተስተባብለዋለ፣ ውሸታም፣  መተተኛ፣ ደጋሚ፣ እብድ.... ተብለዋል።  ፊታቸው ላይ ተተፍቶባቸዋል ለፈጣሪ በመስገድላይ እያሉ ፈርስ ተደፍቶባቸዋል 
  እየሱስ መከራን እንደተቀበለው ሁላ

ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ያልደረሰባቸው የመከራ አይነት የለም ያውም በወገኖቻቸው

    ተሰድበዋል ፣ተደብድበዋል ፣በድንጋይ ተወግረዋል ፣መአቀብ ተጥሎባቸዋል፣የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸዋል ፣ከሀገራቸው ተባረዋል

የተጣለባቸው መአቀብ ለሶስት ዓመታት የቆየ ሲሆን ማንም ሰው ከነብዩ ሙሀመድ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገበያየት በጋብቻ መተሳሰር ማናገር ቤታቸው መግባት የሚከለክል ነበር። አስባችሁታል መተዳደሪያው ንግድ ብቻ ለሆነ ማህበረሰብ ለሶስት ዓመታት መሸጥ መለወጥ ሲከለከል ኑሮ እንዴት እንደሚከብድ። ሚላስ ሚቀመስ አጥተው እንዴት እንደተቸገሩ ።

የመካ ባላባቶች ለ ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ሙሀመድ ሆይ ክብር ፈልገክ ከሆነ የሁላችንም አለቃ እናድርግህ ያላንተ ፈቃድ ምንም አንፈፅምም ንግስናም ፈልገክ ከሆነ ንጉስ አድርገን እንሹምህ ሀብትም ከሆነ ምትፈልገው ያሻህን ያህል ሀብት እንስጥህ ሴትም ፈልገክ ከሆነ ቆነጃጅትን መርጠን እንዳርልህ ታመክም ከሆነ አለ የተባለ ሀኪም አስመጥተን እናሳክምህ(ሀኪሙ ይፈውስህ) አንተ ብቻ #"አላህ ነብይ አድርጎ ልኮኛል አላህን ብቻ አምልኩ ጣዖታትን ራቁ" ምትለውን ተው ብለው መደራደሪያ አቅርበውላቸው ነበር በዚ ግዜ የነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ)መልስ ፀሀይን በቀኝ እጄ ጨረቃን በግራ እጄ ላይ ብታስቀምጡልኝ እንኳን አላህ የላከኝን መልእክት ለሰው ዘር እስከማደርስ ወይም እስከምሞት ድረስ አላርፍም ብለው ነበር የመለሱት።

 ታዲያ ሀሰተኛ ነብይ ቢሆኑ ኖሮ ይህን ሁሉ አለማዊ ጥቅም እምቢ ብለው ያን ሁሉ መከራ ይሸከሙ ነበር ? መልሱን ለናንተው ትቸዋለው 

ሌላም ማባበያ አቅርበውላቸው ነበር እሱም አንተም የኛን ጣዖቶች አምልክ እኛም ያንተን አምላክ እናምልክ መሀል ላይ እንገናኛለን ብለዋቸው ነበር የነብዩ መልስ ለኔም የራሴ እምነት አለኝ ለናንተም የራሳችሁ እምነት አላችሁ የፈለገ ሰው ያሻውን እምነት ይከተል የእምነት ነፃነት ይኑር ብለው ነው የመለሱላቸው።

እየሱስም የሀገሩ ሰዎች ከማመን ሲሰናከሉበት ማርቆስ 6 :4 ኢየሱስም፣ “ነቢይ የማይከበረው በገዛ አገሩ፣ በዘመዶቹ መካከልና በቤተ ሰቡ ዘንድ ብቻ ነው” እንዳለው

ነብዩ ሙሀመድም (ሰ.ዐ.ወ) የገዛ ዘመዶቻቸው እና የሀገራቸው(የመካ) ሰዎች አናምንህም ብለው አስተባብሏቸው ከዚህም አልፈው ሊገድሏቸው ሲሉ በመጨረሻ ተወልደው ያደጉባትን መካን ትተው ወደ መዲና ተሰደዱ የመዲና ነዋሪኦች በመልካም ተቀበሏቸው እዛ አዲስ መሀበረሠብ ማነፅ ጀመሩ ። ኢሄኔ መካውያን መዲና ላይ የንግድ መአቀብ ጣሉባት ይህም ሳይበቃ ጦርነት አወጁባቸው። ይህ ሁሉ መከራ ነብይ በመሆናቸው ነው። እየሱስም የተሰቃየው በዚው ምክንያት ነው።

 ብዙ ሚስቶች ማግባታቸው አላማው የሴት ፍላጎት ቢሆን ኖሮ ልጃገረድ የሆኑትን ብቻ ነበር ሚሰበስቡት። ነገር ግን ከአጠቃላይ ሚስቶቻቸው አንዷ ብቻ ናት ልጃገረድ ሌሎቹ አግብተው የፈቱ ባሎቻቸው የሞቱባቸው እድሜያቸው የገፋ ሴቶች ናቸው።  
አላማው በዘመኑ ከአንድ ጎሳ አባል ጋር በጋብቻ ከተሳሰርክ በአማችነት የተነሳ ያጎሳ ከአንተ ጋር ሰላም ይፈጥራል ከጎንህ ይቆማል ጦርነት አያውጅብህም ። በሌላ ቋንቋ  ለሰላም ሲባል ማለት ነው። ለዚህ እና ሌሎች ምክንያቶች በርካታ ሚስቶችን አግብተዋል። ይህ ባይሆንማ ኖሮ በርካታ ኮረዶችን ብቻ ባገቡ ነበር ። ሁሉም በሚያሰኝ መልኩ የሀገሪቱ ሴቶች (ልጃገረዶች) የነብዩ ሚስት መሆንን  ይመኙ ነበር። ምክንያቱም ፦ ጀግና፣ ቆንጆ፣ የሀገር መሪ፣ የጥሩ ስነ-ምግባር ባለቤት በዚህ ላይ ተወዳጅ ነብይ ነበሩና ነው።

የኛ ከሆነ ከሰል ነጭ ነው ቢልህም ትክክል ነው የነሱ ከሆነ ወተት ነጭ ነው ቢልህም ስተት ነው የሚል አስተሳሰብ አግባብ አይደለም የነገሩንን ብቻ አምኖ መቀበል ሳያሆን እውነቱን ለማወቅ ሁሉንም እውነተነኛ መፅሀፍት በሚዛናዊ አእምሮ በማንበብ አመዛዝኖ እውነታው ላይ መድረስ ነው ያለብን።

እየሱስ ነጣቂ የሆኑ ሀሰተኛ ነብዮች እና ሀሰተኛ ክርስቶሶች እንደሚነሱ መናገሩ እንዲሁም እንዳያስቷችሁ ማለቱ እውነት ነው፡፡

 ነብዩ ሙሀመድም(ሰ.ዐ.ወ) ሀሰተኛ ነብዮች እደሚነሱ ተናግረዋል #አላህ ከኔ በፊት ብዙ ነብያትን ልኳል እኔ የመጨረሻው ነብይ ነኝ ከኔ ቡሀላ ነብይ አይላክም ነገር ግን ሀሰተኞች ነብይ ነኝ ብለው የሚሉ ሰዎች ይነሳሉ ሀሰተኞች ናቸው እንዳታምኟቸው ብለዋል። ያሉትም አልቀረ ነብዩ ሊሞቱ አቅራቢያ ሁለት ሰዎች ነብይ ነኝ ብለው በተለያዩ ቦታዎች ላይ ተነስተው ነበር አሁንም በየ አዳራሹ ነብይ ነኝ ሚሉ ሀሰተኞች ሞልተዋል። ነብይነት ከፈጣሪ የሚሰጥ እንጂ በህዝብ ድምፅ ወይም ነኝ በማለት የሚገኝ አይደለም።  የአላህ ሰላም  በነብዩ ሙሀመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ላይ ይሁን።

አላህም(ፈጣሪ) እንዲህ ሲል ነብይነታቸውን ገልፇል

مَّا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِّن رِّجَالِكُمْ وَلَـٰكِن رَّسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድም ሰው አባት አይደለም፡፡ ግን የአላህ መልክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ (ሱረቱ አል- አሕዛብ - 40)

هُوَ الَّذِي أَرْسَلَ رَسُولَهُ بِالْهُدَىٰ وَدِينِ الْحَقِّ لِيُظْهِرَهُ عَلَى الدِّينِ كُلِّهِ ۚ وَكَفَىٰ بِاللَّهِ شَهِيدًا እርሱ ያ መልክተኛውን በመሪ መጽሐፍና በእውነተኛ ሃይማኖት በሃይማኖት ሁሉ ላይ ሊያልቀው የላከ ነው፡፡ መስካሪም በአላህ በቃ፡፡ (ሱረቱ አል ፈትሕ - 28)

الَّذِينَ كَفَرُوا وَصَدُّوا عَن سَبِيلِ اللَّهِ أَضَلَّ أَعْمَالَهُمْ እነዚያ የካዱ ከአላህ መንገድም የከለከሉ (አላህ) ሥራዎቻቸውን አጠፋባቸው፡፡ (ሱረቱ ሙሐመድ - 1)

وَالَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَآمَنُوا بِمَا نُزِّلَ عَلَىٰ مُحَمَّدٍ وَهُوَ الْحَقُّ مِن رَّبِّهِمْ ۙ كَفَّرَ عَنْهُمْ سَيِّئَاتِهِمْ وَأَصْلَحَ بَالَهُمْ እነዚያም ያመኑ፣ በጎዎችንም የሠሩ፣ በሙሐመድ ላይም የወረደው እርሱ ከጌታቸው ሲኾን እውነት ስለ ኾነ ያመኑ ከእነርሱ ላይ ኃጢአቶቻቸውን ያባብሳል፡፡ ኹኔታቸውንም ሁሉ ያበጃል፡፡ (ሱረቱ ሙሐመድ - 2)

ذَٰلِكَ بِأَنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا اتَّبَعُوا الْبَاطِلَ وَأَنَّ الَّذِينَ آمَنُوا اتَّبَعُوا الْحَقَّ مِن رَّبِّهِمْ ۚ كَذَٰلِكَ يَضْرِبُ اللَّهُ لِلنَّاسِ أَمْثَالَهُمْ ይህ እነዚያ የካዱት ውሸትን የተከተሉ በመኾናቸውና እነዚያም ያመኑት ከጌታቸው የኾነን እውነት ስለተከተሉ ነው፡፡ እንደዚሁ አላህ ለሰዎች ምሳሌዎቻቸውን ያብራራል፡፡ (ሱረቱ ሙሐመድ - 3)