ካይልባድ

ከውክፔዲያ

ካይልባድ343 እስከ 344 ዓም ያሕል ድረስ የ አየርላንድ ከፍተኛ ንጉሥ ነበር።

በአይርላንድ ታሪኮች ዘንድ ቀዳሚውን ሙይረዳቅ ቲረቅን ገድሎ ለአንድ አመት ከፍተኛ ንጉሥነቱን ያዘ፤ ከዚያ በተከታዩ ዮቃይድ ሙግሜዶን ተገደለ።

የቲገርናቅ ዜና መዋዕል (1080 ዓም ተቀነባብሮ) ካይልባድ ሙይረዳቅን የገደለበት ዓመት በ343 ዓም ያደርጋል፤ ከፍተኛ ንጉሥ እንደ ሆነ ግን አይጠቅስም።