ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 7

ከውክፔዲያ

ታኅሣሥ ፯

  • ፲፱፻፷፪ ዓ/ም የብሪታንያ የሕዝብ ተወካዮች ሸንጎ የነፍሰ ገዳዮችን የሞት ቅጣት በህግ ሰረዘ።
  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ኃይል እየተዳከመ በአንጻሩ ደግሞ ተቃዋሚዎቻቸው እያደር እየጎለመሱ መሄዳቸውን የተገነዘቡት ሽብርተኞች በቁጥጥራቸው ላይ የነበሩትን ሃያ መሳፍንት፣ መኳንንት፣ ሚኒስትሮችንና መኮንኖችን ወደ አረንጓዴ ሳሎን ያዛውሩና አልጋወራሹንና አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ለብቻቸው እንዲጠበቁ ያደርጋሉ። ጄነራል ጽጌ ዲቡ ወዲያው ከተቃራኒ ወገን በተተኮሰ ጥይት ሲገደሉ፣ እነ ጄነራል መንግሥቱ የያዟቸውን እስረኞት ረሽነው ለማምለጥ ወስነው ሜጄር ጄኔራል ሙሉጌታ ቡሊ፤ ራስስዩም መንገሻ፤ ራስ አበበ አረጋይ፤ አቶ መኮንን ሀብተወልድአባ ሐና ጅማ፤ በጠቅላላው አሥራ አምስት ሰዎች ተረሽነው ሞቱ። የክብር ዘበኛ መኮንን የነበሩት ሻምበል ደረጀ ኃይለ ማርያም ሽብርተኞቹን በመቃወም የቤተ መንግሥቱን አጥር በታንክ ደምስሰው ሲገቡ ከሽብርተኞት ወገን በተተኮሰ ጥይት ተገደሉ። ሻምበል ደረጀ የስመ ጥሩው አርበኛ የኃይለ ማርያም ማሞ ልጅ እና የንጉሠ ነገሥቱ የልጅ ልጅ የልዕልት ሶፊያ ደስታ ባል ነበሩ።
  • ፳፻፫ ዓ/ም የኢትዮጵያና የቅዱስ ጊዮርጊስ ቡድኖች እግር ኳስ ተጫዋችና አሰልጣኝ የነበረው በኩሩና ኮከቡ መንግሥቱ ወርቁ፣ በ፸ ዓመቱ አረፈ። መንግሥቱ ወርቁ በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች የፍጻሜ ግጥሚያዎች የተሳተፈ ሲሆን፣ በ፫ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ግብፅን ፬ ለ ፪ አሸንፋ ዋንጫ እንድታገኝ ሁለቱን ግቦች ያስቆጠረና በዚሁ በ፫ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፫ ግብ በማስቆጠሩም የኮከብ ግብ አግቢነት ክብር አግኝቷል፡፡