የሐዋርያት ሥራ ፳፰

ከውክፔዲያ
የሐዋርያት ሥራ ፳፰
የዋርያት ሥራ ፲፭ ፳፪ ፳፬ በኮዴክ ላውዲያነስ (Codex Laudianus) በ፭፻፶ ዓ ም የተጻፈ
አጭር መግለጫ
ፀሐፊ ቅዱስ ሉቃስ
የመጽሐፍ ዐርስት የሐዋርያት ሥራ
የሚገኘው በአዲስ ኪዳን ፭ኛው መጽሐፍ
መደብ የቤተክርስቲያን ታሪክ
ቅዱስ ጳውሎስ በፑፕልዮስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ እንደጸለየለት


ቁጥር ፳፰ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የመጨረሻው ምዕራፍ ሲሆን ይዘቱ የጳውሎስን ጉዞ በተለይ ከማልታ ወደ ጣልያን ከዞም በሮም መርጋቱን የሚገልጽ ነው ። የጻፈውም ቅዱስ ሉቃስ እንደሆነ በማስረጃ ሙሉበሙሉ ቤተክርስቲያን የምታምነው ነው ።

ኢየሩሳሌም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቢየሩሳሌም
እስራኤል
ቅዱስ ሉቃስ የሐዋርያትን ሥራ የጻፈባት ቅድስት ከተማ ኢየሩሳሌምናዝሬት


ስለ ፅሑፉ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የመጀመሪያው ፅሑፍ በኮይን ግሪክ ሲፃፍ በ፴፩ ንዑስ ክፍል የተከፈለ ነው ። በጣም ጥንት ከሚባሉ እነዚህን ክፍሎች የሚይዙ ፅሑፎች የሚከተሉት ናቸው ፡

  • ወደ ግዕዝ የተተረጎመው ማለትም መጸሐፍ ቅዱስ ከዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ ሲተረጎም የነበረው ፅሑፍ
  • Codex Vaticanus 325-350 ዓ.ም.እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር
  • Codex Sinaiticus 330-360 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር
  • Codex Bezae 400 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር
  • Codex Alexandrinus 400-440 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር
  • Codex Ephraemi
  • Rescriptus 450 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር (ቁጥር ፩-፬)
  • Codex Laudianus 550 ዓ.ም.(ቁጥር ፳፯-፴፩)

የተጠቀሱ ቦታዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ተግባራቱ የተፈፀሙበት ቦታዎችን በቅደምተከተል እንደሚከተለው ይነበባሉ

ቁጥር ፰[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በዚህ ምዕራፍ የግዕዝ ጽሑፉ የሚጨምረው አለ ይህም ምንድንነው "ጳውሎስም ወደ እርሱ ገብቶ ጸለየለት እጁንም በላዩ ጭኖ ፈወሰው።" የሚለው ነው ። በዚህም ምክኒያት ፑፕልዮስም ልጁም በጳውሎስ ላይ ልዩ የአምላክ ኃይል እንዳለበት እንዲያምኑ አረጋቸው ።



የሐዋርያት ሥራ ፳፰[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቁጥር ፩ - ፲[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

1 በደኅና ከደረስን በኋላ በዚያን ጊዜ ደሴቲቱ መላጥያ እንድትባል አወቅን። 2 አረማውያንም የሚያስገርም ቸርነት አደረጉልን፤ ዝናብ ስለ ሆነም ስለ ብርዱም እሳት አንድደው ሁላችንን ተቀበሉን። 3 ጳውሎስ ግን ብዙ ጭራሮ አከማችቶ ወደ እሳት ሲጨምር እፉኝት ከሙቀት የተነሣ ወጥታ እጁን ነደፈችው። 4 አረማውያንም እባብ በእጁ ተንጠልጥላ ባዩ ጊዜ፥ እርስ በርሳቸው፦ ይህ ሰው በእርግጥ ነፍሰ ገዳይ ነው፥ ከባሕርም ስንኳ በደኅና ቢወጣ የእግዚአብሔር ፍርድ በሕይወት ይኖር ዘንድ አልተወውም አሉ። 5 እርሱ ግን እባቢቱን ወደ እሳት አራገፋት አንዳችም አልጐዳችውም፤ 6 እነርሱም፦ ሊያብጥ ወይም ወዲያው ሞቶ ሊወድቅ ነው ብለው ይጠባበቁት ነበር ብዙ ጊዜ ግን ሲጠባበቁ በእርሱ ላይ የሚያስገርም ነገር ምንም ባላዩ ጊዜ፦ ይህስ አምላክ ነው ብለው አሳባቸውን ለወጡ። 7 በዚያም ስፍራ አጠገብ ፑፕልዮስ የሚሉት የደሴት አለቃ መሬት ነበረ፥ እርሱም እንግድነት ተቀብሎን ሦስት ቀን በፍቅር አሳደረን። 8 የፑፕልዮስም አባት በንዳድና በተቅማጥ ታሞ ተኝቶ ነበር፤ ጳውሎስም ወደ እርሱ ገብቶ ጸለየለት እጁንም በላዩ ጭኖ ፈወሰው። 9 ይህም በሆነ ጊዜ የቀሩት ደግሞ በደሴቲቱ ደዌ የነበረባቸው እየመጡ ተፈወሱ፤ 10 በብዙ ክብርም ደግሞ አከበሩን፥ በተነሣንም ጊዜ በመርከብ ላይ የሚያስፈልገንን ነገር አኖሩልን።

ቁጥር ፲፩ - ፳[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

11 ከሦስት ወርም በኋላ በደሴቲቱ ከርሞ በነበረው በእስክንድርያው መርከብ ተነሣን፥ በእርሱምየዲዮስቆሮስ አላማ ነበረበት። 12 ወደ ሰራኩስም በገባን ጊዜ ሦስት ቀን ተቀመጥን፤13 ከዚያም እየተዛወርን ወደ ሬጊዩም ደረስን። ከአንድ ቀን በኋላም የደቡብ ነፋስ በነፈሰ ጊዜ በሁለተኛው ቀን ወደ ፑቲዮሉስ መጣን። 14 በዚያም ወንድሞችን አግኝተን በእነርሱ ዘንድ ሰባት ቀን እንድንቀመጥ ለመኑን፤ እንዲሁም ወደ ሮሜ መጣን። 15 ከዚያም ወንድሞች ስለ እኛ ሰምተው እስከ አፍዩስ ፋሩስና ሦስት ማደሪያ እስከሚባለው ሊቀበሉን ወጡ፥ ጳውሎስም ባያቸው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነ ልቡም ተጽናና። 16 ወደ ሮሜም በገባን ጊዜ ጳውሎስ ከሚጠብቀው ወታደር ጋር ለብቻው ይቀመጥ ዘንድ ተፈቀደለት። 17 ከሦስት ቀንም በኋላ ጳውሎስ የአይሁድን ታላላቆች ወደ እርሱ ጠራ፤ በተሰበሰቡም ጊዜ እንዲህ አላቸው፦ ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ሕዝቡን ወይም የአባቶችን ሥርዓት የሚቃወም አንዳች ሳላደርግ፥ ከኢየሩሳሌም እንደ ታሰርሁ በሮማውያን እጅ አሳልፈው ሰጡኝ። 18 እነርሱም መርምረው ለሞት የሚገባ ምክንያት ስላልነበረብኝ ሊፈቱኝ አሰቡ፤ 19 አይሁድ ግን በተቃወሙ ጊዜ፥ ወደ ቄሣር ይግባኝ እንድል ግድ ሆነብኝ እንጂ ሕዝቤን የምከስበት ነገር ኖሮኝ አይደለም። 20 ስለዚህም ምክንያት አያችሁና እነግራችሁ ዘንድ ጠራኋችሁ፤ ስለ እስራኤል ተስፋ ይህን ሰንሰለት ለብሻለሁና።

ቁጥር ፳፩ - ፴፩[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

21 እነርሱም፦ እኛ ከይሁዳ ስለ አንተ ደብዳቤ አልተቀበልንም፥ ከወንድሞችም አንድ ስንኳ መጥቶ ስለ አንተ ክፉ ነገር አላወራልንም ወይም አልተናገረብህም። 22 ነገር ግን ስለዚህ ወገን በየስፍራው ሁሉ እንዲቃወሙ በእኛ ዘንድ ታውቆአልና የምታስበውን ከአንተ እንሰማ ዘንድ እንፈቅዳለን አሉት። 23 ቀንም ቀጥረውለት ብዙ ሆነው ወደ መኖሪያው ወደ እርሱ መጡ፤ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም እየመሰከረ ስለ ኢየሱስም ከሙሴ ሕግና ከነቢያት ጠቅሶ እያስረዳቸው፥ ከጥዋት ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ ይገልጥላቸው ነበር። 24 እኵሌቶቹም የተናገረውን አመኑ፥ እኵሌቶቹ ግን አላመኑም፤ 25 እርስ በርሳቸውም ባልተስማሙ ጊዜ፥ ጳውሎስ አንዲት ቃል ከተናገረ በኋላ ሄዱ፤ እንዲህም አለ፦ መንፈስ ቅዱስ በነቢዩ በኢሳይያስ ለአባቶቻችን፦ 26 ወደዚህ ሕዝብ ሂድና፦ መስማትን ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ ማየትንም ታያላችሁና አትመለከቱም፤ 27 በዓይናቸው እንዳያዩ በጆሮአቸው እንዳይሰሙ በልባቸውም እንዳያስተውሉ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአል ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል በላቸው ሲል መልካም ተናገረ። 28 እንግዲህ ይህ የእግዚአብሔር ድኅነት ለአሕዛብ እንደ ተላከ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፤ እነርሱ ደግሞ ይሰሙታል። 29 ይህንም በተናገረ ጊዜ አይሁድ እርስ በርሳቸው እጅግ እየተከራከሩ ሄዱ። 30 ጳውሎስም በተከራየው ቤት ሁለት ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፥ ወደ እርሱም የሚመጡትን ሁሉ ይቀበል ነበር፤ 31 ማንም ሳይከለክለው የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበከ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እጅግ ገልጦ ያስተምር ነበር።