Jump to content

የሸክላ ማጫወቻ

ከውክፔዲያ
የ1960ዎች ሸክላ ማጫወቻ እና ራዲዮን

የሸክላ ማጫወቻ በቀድሞው ክፍለ ዘመን አይነተኛ የሙዚቃ ወይም ድምጽ ማጫወቻ ዘዴ ነበር።

ኤዲሶን እና አዲስ ፍጥረቱ ፎኖግራፉ በ1870 ዓም

መጀመርያ በ1870 ዓም በአሜሪካዊቶማስ ኤዲሶን ተፈጥሮ «ፎኖግራፍ» ሲባል ድምጹ የተቀረጸበት በሰም ወረቀት ላይ ነበር። በጊዜ ላይ አሠራሩ በጣም ተሻሽሎ ድምጾች በሙዚቃ ሸክላ ላይ ይቀረጹ ነበር።

1980ዎቹ ጀምሮ ግን አዳዲስ ፈጠራዎች እንደ ካሴት ወይም ሲዲ ተገኝተው የሸክላ ማጫወቻ ጥቅም በአሁኑ ሰዓት እጅግ ተቀንሷል።