የዛር መንፈስ

የዛር መንፈስ የአእምሮ ስራንና ንቃተ ህሊናን የሚረብሽ በሽታ ሲሆን የሰው ልጅ አካሉ በእርኩስ መንፈስ፣ ሰይጣን ወይም ዲያብሎስ ሲጠቃ ይመጣል ተብሎ ይታመናል።[1] የዛር መንፈስ ከአእምሮ በሽታ የሚለየው የአካልና አእምሮ መረበሹ ለአጭር ጊዜ የሚቆይ መሆኑ እና ከባህል ጋር የተቆራኘ መሆኑ ነው። የዛር መንፈስ አስተሳሰብ በብዙ ባህሎች እና ሀይማኖቶች የተስፋፋ ነው። ለምሳሌ ያህል በክርስትና፣ እስልምና፣ በአይሁድ፣ ቡድሂዝም እንዲሁም በአፍሪካና ኢዥያ ነባር ባህላዊ ሃይማኖቶች በሰፋት ይታወቃል። [2] በ1969 በአሜሪካ ብሔራዊ የአእምሮ ጤና ኢንስቲትዩት በተደረገ ጥናት፣ በሁሉም የዓለም ክፍሎች ከሚገኙት 488 ማህበረሰቦች ውስጥ 74%ቱ የዛር መንፈስ እንዳለ ያምናሉ። [3][4]

በክርስትና ዛር ከዲያብሎስ (ማለትም ከሰይጣን ) እና ከአጋንንት እንደሚመጣ ይታመናል። አማኞቹ ሰይጣን መንፈሳዊ በሽታዎችን በሰው ልጅ አካልና አእምሮ ላይ ያመጣል ብለው ያምናሉ።[5] መስቅል፣ መጽሃፍት፣ ጾም፣ ጸሎት፣ ጸበል እና የተለያዩ ዘይቶች ዛሩን ከሰውነት ለማስወጣት ጥቅም ላይ ይውላሉ።

አዲስ ኪዳን ኢየሱስ አጋንንትን ከሰዎች ያስወጣባቸውን በርካታ ክፍሎች ይጠቅሳል። [6] አብዛኞቹ ክርስቲያኖች ዛር ያለፈቃድ የሚመጣ መከራ ነው ብለው ቢያምኑም፣ [7] አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ይዞታ በፈቃደኝነት ሊሆን እንደሚችልም ይጠቁማሉ። ለምሳሌ፣ በዮሐንስ ወንጌል 13 ፡27 ላይ ሰይጣን በአስቆሮቱ ይሁዳ ውስጥ ሊገባ የቻለው ይሁዳ ያለማቋረጥ ሰይጣን ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጥ ያቀረበውን ሃሳብ ተቀብሎ ሙሉ በሙሉ ስለተገዛለት ነው የሚሉ አሉ። [8]
አዲስ ኪዳን ሰዎች በአጋንንት ሊያዙ እንደሚችሉ፣ ነገር ግን አጋንንት ለኢየሱስ ክርስቶስ ሥልጣን እንደሚገዙ ይጠቁማል። ለምሳሌ ሉቃ 4፣ 33 - 35፣ ማቴ 8፣ 28 - 34። የጌራሴኔን አጋንንት ማስወጣት አጋንንት እንስሳትን ሊይዙ እንደሚችሉም ያመለክታል። ሉቃስ 8፡26-37። ከዚህ በተጨማሪ የወንጌል ጽሑፎች መግደላዊት ማርያም አጋንንትን እንደወጣላት ይናገራሉ።
በእስላማዊ ባህል ውስጥ የሚገኙት እንደ ጂን ፣ ሻያቲን ፣ አፋሪት ያሉ የተለያዩ ፍጥረታት ብዙውን ጊዜ ከዛር መንፈስ ጋር የተያያዙ ናቸው። የዛር መንፈስ በእስላማዊ ሥነ-መለኮት እንዲሁም በባህላዊ ትውፊቶች ውስጥ በሰፊው የሚታወቅ ጉዳይ ነው።
አንዳንድ የሙስሊም ሊቃውንት ባይቀበሉትም በመቃብር ወስጥ ወይም በመቃብር አጠገብ መተኛት እንቅልፍ የተኛን ሰው በህልም ከሚጎበኙ እና የተደበቀ እውቀት ከሚሰጡት የሙታን መናፍስት ጋር መገናኘት ያስችላል ተብሎ ይታመናል። [9] በአፋሪት (የበቀል መንፈስ) የተያዙ ሰዎች ልእለ ሰው እንደሚሆኑ ወይም ሊያብዱም እንደሚችሉ ይነገራል።[10]
በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተከለከለ ቢሆንም ፣ አስማት በሁለተኛው የቤተመቅደስ ጊዜ በሰፊው ይሠራ ነበር። ቤተመቅደሱ ከፈረሰ ጀምሮ ባሉት ጊዜያት በ 3 ኛ ፣ 4 ኛው እና 5ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በኋላ ይዘወተር እንደነበር በጥልቀት ተመዝግቧል ። በአይሁድ ሃይማኖት ዛር የማስወጣት ዘዴዎች በመጽሐፈ ጦቢት በሰፊው ተገልጸዋል። [11]

ለአብነት በጉራጌ ሕዝብ ዘንድ የዛር መንፈስ የታወቀ የመንፈስ በሽታ ነው። የዛሩ አይነት እንደ ጾታው ይለያያል። ለምሳሌ በወንዶች ላይ ብቻ የሚከሰት የዛር በሽታ መንስኤው አውሬ ተብሎ በሚጠራው መንፈስ እንደሆነ ይታመናል። ህመምተኛው የምግብ ፍላጎት ማጣት፣ ማቅለሽለሽ እና ከባድ የሆድ ህመም ያጠቃዋል። ከዚህ በተጨማሪ፣ ድንዛዜ፣ ማንቀጥቀጥ እና ከፊል እጅና እግር ሽባ መሆን ይታያሉ።[12]
ተጎጂው እንዲሁ ካላገገመ ዛር ጠሪው ወይም ሳግዋራ ይጠራሉ። ሳግዋራ የመንፈሱን ስም ከወሰነ በኋላ፣ መንፈሱን ለማስወጣት መድሃኒት ይቀምማል። ይህ መድሀኒት ግን ሰውየውን አይፈውሰውም። የዛር መንፈሱ ተመልሶ ይይዘዋል ስለሚባል መድሃኒቱን እድሜ ልኩን ይወስዳል። ተጎጂው ከመንፈሱ ጋር ግንኙነት እንዲፈጥርና እርቅ እንዲፈጥር ይደረግጋል። መድሃኒቱ በእንሰት፣ ቅቤና አዋዜ የሚወሰድ ነው። [12]
አንትሮፖሎጂስት አይኤም ሉዊስ ሴቶች ከወንዶች ይልቅ በዛር መንፈስ የመጠቃት እድላቸው ሰፊ ነው። ለዚህም ምክኒያቱን ሲያስቀምጥ ሴቶች በብዙ ዘርፎች በወንዶች ስለተገለሉና ስለተጨቆኑ ትኩረትና ድጋፍ ለማግኘት ማካካሻ መንገዳቸው ነው።[13]
ሌላዋ አንትሮፖሎጂስት አሊስ ቢ ኬሆ እና ዶዲ ኤች ጊሌቲ ሴቶች በዛር መንፈስ የሚጠቁት በቲያሚን፣ ትሪፕቶፋን፣ ኒያሲን ፣ ካልሲየም እና ቫይታሚን ዲ እጥረት ምክንያት እንደሆነ ይከራከራሉ። ድህነት እና የምግብ እጥረት ይህንን ችግር እንደሚፈጥሩ እና እርግዝና እና ጡት ማጥባት ደግሞ ችግሩን እንድሚያባብሰው ይገልፃሉ። ዛር በብዛት ጥራጥሬ ማሽላ እና በቆሎ በሚበላባቸው እና ዝቅተኛ የፕሮቲንና መሰል ንጥረ ምግቦች በሚታይቸው ማህረሰቦች ዘንድ ይበረታል። ከዚህ በተጨማሪ ሴቶች በማህረሰቡ ዘንድ ትንሽ እንዲበሉ ያለው ጫና፣ ከሁሉም በሁዋላ እንዲበሉ መደረጋቸውና መሰል ልምዶች ለምግብ እጥረት ይዳርጋቸዋል። የዛር መንፈስ በአመዛኙ የድሃዎች በሽታ መሆኑ ሲታይ የንጥረ ምግብን ቲዎሪ ይበልጥ ያጠናክራል። በዛር ባህላዊ ህክምና (ጅብጅባ) ባለአውሊያው ዛሩን አስነስቶ ስሙንና ፍላጎቱን ሲጠይቀው በብዛት መልሱ የእንስሳት እርድ፣ ጊጣጌጥና ልብስ ነው። ባለዛሮች በጅብጀባው ወይም ሀይማኖታዊ የፈውስ ስርዓት ወቅት የሚያሳዩት የሰውነት እንቅስቃሴ፣ የአእምሮና ንግግር ለውጥ ከአገር አገር መለያየቱ ሰው የዛር መንፈስ ስርዓትን በኑሮው ከህብረተሰብ ወይም ከሚዲያ እንደሚማረው ያሳያል። የዛር መንፈስ ለጀብጃቢው ወይም ለአጥማቂው ስልጣን መታዘዙ Hypnosis ወይም የመንፈሳዊ ሰመመን ስልትን የተከተለ ነው።[14]
የዛር መንፈስ በክሊኒካል ሳይካትሪ መሰረት ለአጭር ጊዜ የሚቆይ ማንነትን እና አካባቢን መርሳት፣ መልቀቅ እና የአእምሮ መሰወር ነው። እንደ አንድ dissociative ዲስኦርደር አይነት ይታያል። [15]
በዛር መንፈስ ተይዘዋል የተባሉ ሰዎች [16] ከአእምሮ ሕመም ምልክቶች ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው ምልክቶችን ለምሳሌ ከሃቅ መውጣት derealization ፣ የተሳሳተ ስሜት Hallucination፣ እብደት Psychosis፣ ሚጥል በሽታ ወዘተ ሊያሳዩ ይችላሉ። [17] የዛር መንፈስ ባለፈ ጉዳት ምክንያት (አስገድዶ መደፈር፣ መገለል፣ መረሳት፣ የቤተሰብ ችግር ወዘተ) ሊመጡ እንደሚችሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ።[18]
የዛር መንፈስ በሽታ ባህላዊ የአእምሮ በሽታ እንደመሆኑ የሳይካትሪ መድሃኒቶች አያስፈልጉትም። ህክምናው ባህላዊ፣ መንፈሳዊና የሳይኮሎጅ ህክምና ነው። ስልቱም Hypnosis ይባላል። በዚህ ህክምና መንገድ እስከ 59% ተጠቂዎች ከበሽታው ይፈወሳሉ። የዛር መንፈስ በሽታ በወቅቱ ካልታከመ አካላዊ በሽታ (Somatization) ሊያስከትል ይችላል። ለምሳሌ የልብ ችግር፣ የጨጉዋራ እና የሳንባ ችግር። [19]
- ↑ Jones (2005), p. 8687.
- ↑ Van Eyghen, Hans (14 April 2023). The Epistemology of Spirit Beliefs. Routledge Studies in the Philosophy of Religion. Routledge. pp. 118, 127. ISBN 9781003281139. https://www.taylorfrancis.com/books/oa-mono/10.4324/9781003281139/epistemology-spirit-beliefs-hans-van-eyghen. "Regarding an experience as a possession-experience can serve a psychological need and be veridical at the same time. [...] [...] possession-experiences [...] can [...] provide prima facie justification for a set of beliefs regarding spirits and their natures.]"
- ↑ Jones (2005), p. 8687.
- ↑ Bourguignon & Ucko (1969).
- ↑ Van Eyghen, Hans (14 April 2023). The Epistemology of Spirit Beliefs. Routledge Studies in the Philosophy of Religion. Routledge. pp. 118, 127. ISBN 9781003281139. "Regarding an experience as a possession-experience can serve a psychological need and be veridical at the same time. [...] [...] possession-experiences [...] can [...] provide prima facie justification for a set of beliefs regarding spirits and their natures.]"
- ↑ "The New Testament" (2011).
- ↑ Malachi (1976), p. 462.
- ↑ "John 13:27".
- ↑ Diem & Schöller (2004), p. 144.
- ↑ Diem & Schöller (2004), p. 144.
- ↑ "Demons and demonology" (2008).
- 1 2 Shack (1971), pp. 40–43.
- ↑ Lewis (1966), pp. 307–329.
- ↑ Kehoe & Giletti (1981), pp. 549–561.
- ↑ Bhavsar, Ventriglio & Dinesh (2016), pp. 551–559.
- ↑ "How Exorcism Works" (8 September 2005).
- ↑ Strickmann (2002), p. 65.
- ↑ Braitmayer, Hecker & Van Duijl (2015).
- ↑ Karanci (2014).