ደላንታ
Appearance
የደላንታ ወረዳ በአማራ ክልላዊ መንግስት ዉስጥ በደቡብ ወሎ ዞን ከሚገኙት 24 ወረዳዎች አንዷ ስትሆን በሰሜን - ዋድላና ጉባ ላፍቶ በደቡብ - ተንታ በምዕራብ - ዋድላ በምስራቅ - አምባሰል ወረዳ ያዋስኗታል ፡፡ ወረዳዋ በ31 የገጠር ቀበሌዎችና በ2 የከተማ ቀበሌ የተከፈለች ናት፡፡ ከወረዳው ህዝብ ብዛት 97% በግብርና ዘርፍ የተሰማራ ሲሆን 3% ደግሞ በመንግስት ስራና በንግድ ዘርፍ የተሰማራ ነው፡፡ ወረዳዋ በክልሉ ከሚገኙ ዝናብ አጠር ወረዳዎች አንዱ ስትሆን በዋናነት የሚመረቱ ሰብሎች ስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ. ማሺላ፣ ጓያ
ጤፍ፡ ምስርና ሺምብራ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ የአባይ ወንዝ ገባር የሆነው የበሽሎ ወንዝ ወረዳዋን ከተንታ ወረዳ ጋር ያዋስናታል፡፡ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሀገራችን በረዝማኔው የመጀመርያው የሆነው የበሽሎ ድልድይ ሁለቱን ወረዳዎች ክረምት
ከበጋ ከማገናኘቱም ባለፈ በቀጣይ ከአለም ገና ሰቆጣ ለሚገነባው ሀገር አቋራጭ መንገድ ታስቦ የተሰራ ነው፡፡ ዥጣ ደግሞ ወረዳዋን ከዋድላ ወረዳ የሚያዋስናት ሌለኛው ትልቅ ወንዝ ነው፡፡
ስልክ ከአዲስ አበባ ያለው ርቀት ከባህር ዳር ያለዉ ርቀት ከደሴ ያለው ርቀት ህዝብ ብዛት ስፋት (ስኩዌር ኪሜ)
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |