ዲማ

ከውክፔዲያ
ዲማ
ከፍታ 2,076 ሜትር
ዲማ is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
ዲማ

10°0′ ሰሜን ኬክሮስ እና 38°29′ ምሥራቅ ኬንትሮስ


ዲማምስራቅ ጎጃምእነማይ ወረዳ የሚገኝ ከተማ ነው። ይህ ቦታ በተለይ እውቅና እሚያገኘው የዲማ ጊዮርጊስን ቤተክርስቲያንና መናኞችና ሌሎች የሚጠለሉበት ገዳም በማቀፉ ነው።

በዓፄ ሱሰንዮስ ዘመን የነበሩትን ዓፄ ያዕቆብን ደግፈው ሲዋጉ በጎል ጦርነት ድል የሆኑት ራስ አትናቴዎስ በዲማ ገዳም እንደተጠለሉ በዚያው ዘመን የተጻፉ ድርሳናት ይገልጻሉ[1]። እንዲሁ ደጃዝማች ጎሹ ዘውዴ ልጃቸው ብሩ ጎሹ ሲያምጽ በዲማ ገዳም እንደተጠለሉ እንግሊዙ ሲ ቲ ቤኬ ዘግቦት ይገኛል።

በ19ኛው ክፍለ ዘመን፣ የዲማ ጊዮርጊስጎጃም ውስጥ ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነበር[2]። ቤተ ክርስቲያኑ በ2 ሜትር ከፍታ የድንጋይ አጥር የታጠረ ሲሆን ውስጡ ብዙ ታሪካዊ መጻሕፍትን አካቶ ይዟል። በ1513 ዓ.ም. በአውሮጳውያን ስልት የተሳሉ የዓፄ ናዖድ እና ዓፄ ልብነ ድንግል ምስሎች በቤተርክስቲያኑ በሚገኙ መጽሐፍት ይታያሉ[3]

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ James Bruce, Travels to Discover the Source of the Nile (1805 edition), vol. 3, p. 280
  2. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2011-06-12. በ2012-02-09 የተወሰደ.
  3. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2011-06-12. በ2012-02-09 የተወሰደ.