ዳሞት ውይዴ

ከውክፔዲያ

ዳሞት ወይዴ ወላይታ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች አንዱ ነው። ወረዳው በስተምዕራብ በሶዶ ዙሪያ ወረዳ፥ በበስተሰሜን በድጉና ፋንጎ ወረዳ፥ በስተሰሜን ምሥራቅ በዳሞት ጋሌ ውረዳ፥ እንዲሁም ደግሞ በበስተደቡብ በሁምቦ ወረዳ ይዋሰናል።

የህዝብ ቁጥር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በ1999 ዓ.ም በማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በተደረገው ህዝብ ቆጠራ መሰረት በወረዳው በአጠቃላይ 91,602 ሰው የሚኖር ሲሆን፥ ከነዚህም 44,861 ወንድ ሲሆኑ 46,741 ደግሞ ሴት ናቸው፤ ከ5,300 የሚበልጡ ማለትም 5.79% የምሆኑት በከተማ ይኖራሉ። በዴሳ የወረዳዉ ዋና መቀመጫ ነው። የሚበዙት የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ሲሆኑ፥ 77.03% ያህሉን ይይዛሉ፤ 17.08% የሚሆኑት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያን፥ 4.51% የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና 1.06% የእስልምና እምነት ተከታይ ናቸው።[1]

ዋቢ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ Census 2007 Tables: Southern Nations, Nationalities, and Peoples' Region Archived ኖቬምበር 13, 2012 at the Wayback Machine, Tables 2.1, and 3.4.