Jump to content

ገበታ ሚድያ

ከውክፔዲያ
ገበታ ሚድያ gebeta.net
ስዕል:Gebeta Media Logo.png
ኢንዱስትሪ ሚድያ
የምስረታ_ቦታ ኦስሎ ኖርዌይ
ምርቶች ሳይንስ ዜናዎች፣ መጻሕፍት፣


ገበታ ሚዲያ (እንግሊዝኛ፡ Gebeta Media) መቀመጫውን በኦስሎ፣ ኖርዌይ ያደረገ እና የአፍሪካ ቀንድን ማዕከል ያደረጉ ይዘቶችን የሚያቀርብ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ እና የዕውቀት ማስፋፊያ ዲጂታል መድረክ ነው። ተቋሙ በኖርዌይ የንግድ ሕግ መሠረት Gebeta Media AS በሚል ስም በሕጋዊ መንገድ የተመዘገበ ሲሆን፣ ሳይንሳዊ ዕውቀትን በአማርኛ፣ በትግርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች ተደራሽ ያደርጋል። [1]

"ገበታ" የሚለው ስም በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ባህል ውስጥ ምግብ በጋራ የሚቀርብበትን ዓውድ የሚያመለክት ሲሆን፣ ይህም "ዕውቀትን ለሁሉም በጋራ ማቅረብ" የሚለውን የተቋሙን ፍልስፍና ይወክላል። የተቋሙ መሪ መፈክር "ዕውቀት አጥር ሊኖረው አይገባም" (እንግሊዝኛ፡ Knowledge should have no gatekeeper) የሚል ነው።

ገበታ ሚዲያ በ2008 ዓ.ም. (2016 እ.ኤ.አ.) እንደ ግል የሳይንስ ብሎግ እና የውይይት መድረክ (Forum) ተጀመረ። በአሁኑ ወቅት ተቋሙ በኖርዌይ መንግሥት የታወቀ ሕጋዊ የዲጂታል ሚዲያ ተቋም በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

ውጫዊ መያያዣዎች

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]