ገበታ ሚድያ
Appearance
| ገበታ ሚድያ | gebeta.net | |||
|---|---|---|---|---|
| ስዕል:Gebeta Media Logo.png | ||||
| ኢንዱስትሪ | ሚድያ | |||
| የምስረታ_ቦታ | ኦስሎ ኖርዌይ | |||
| ምርቶች | ሳይንስ ዜናዎች፣ መጻሕፍት፣ | |||
ገበታ ሚዲያ (እንግሊዝኛ፡ Gebeta Media) መቀመጫውን በኦስሎ፣ ኖርዌይ ያደረገ እና የአፍሪካ ቀንድን ማዕከል ያደረጉ ይዘቶችን የሚያቀርብ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ እና የዕውቀት ማስፋፊያ ዲጂታል መድረክ ነው። ተቋሙ በኖርዌይ የንግድ ሕግ መሠረት Gebeta Media AS በሚል ስም በሕጋዊ መንገድ የተመዘገበ ሲሆን፣ ሳይንሳዊ ዕውቀትን በአማርኛ፣ በትግርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች ተደራሽ ያደርጋል። [1]
"ገበታ" የሚለው ስም በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ባህል ውስጥ ምግብ በጋራ የሚቀርብበትን ዓውድ የሚያመለክት ሲሆን፣ ይህም "ዕውቀትን ለሁሉም በጋራ ማቅረብ" የሚለውን የተቋሙን ፍልስፍና ይወክላል። የተቋሙ መሪ መፈክር "ዕውቀት አጥር ሊኖረው አይገባም" (እንግሊዝኛ፡ Knowledge should have no gatekeeper) የሚል ነው።
ገበታ ሚዲያ በ2008 ዓ.ም. (2016 እ.ኤ.አ.) እንደ ግል የሳይንስ ብሎግ እና የውይይት መድረክ (Forum) ተጀመረ። በአሁኑ ወቅት ተቋሙ በኖርዌይ መንግሥት የታወቀ ሕጋዊ የዲጂታል ሚዲያ ተቋም በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።