ጣልያንኛ

ከውክፔዲያ

ጣልያንኛጣልያን ሃገር ብሄራዊ የመግባቢያ ቋንቋ ነው። በጣልያን ብቻ 60 ሚሊዮን ዋና ተናጋሪዎች ሲኖሩት በውጭ ሃገር 10 ሚሊዮን ተናጋሪዎች አሉት። በአጠቃላይ 70 ሚሊዮን ዋና ተናጋሪዎች እና ከ125 ሚሊዮን በላይ ሰዎች እንደ የውጭ ቋንቋቸው ይናገሩታል። ለምሳሌ በዋናነት ስዊትዘርላንድ ውስጥ ከሚነገሩ አራት ትልልቅ ቋንቋዎች አንዱ ነው። ቋንቋው በግሪክሊቢያክሮሽያ እና ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች በጣልያን ቅኝ ግዛት ውስጥ የነበሩ ሃገሮችም ውስጥ ቀላል የማይባሉ ተናጋሪዎች አሉት። በዋና ተናጋሪ ብዛት ከአለማችን 20ኛ ደረጃን ይይዛል።[1]

ዋቢ መጻሕፍት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ Berloco 2018