ጥቁር እንጨት

ጥቁር እንጨት (Prunus africana) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።
የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ልጡ በአፍሪካዊ ባህሎች ስለሚፈለግ፣ የሚያሳስብ አደጋ ሁኔታ አለው፤ በካሜሩንም ለዚህ ጥቅም ታርሷል።
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
በሰፊ ከመካከለኛ እስከ ደቡባዊ አፍሪካ ይገኛል።
የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
እንጨቱ ጽኑ ነውና ለሳንቃ ይጠቀማል።
ቅጠሎቹ ለቁስል ፋሻ እንደ ተጠቀሙ ተብሏል።[1]
በልዩ ልዩ አፍሪካዊ አገራት ባህላዊ መድሃኒቶች ውስጥ ረጅም ታሪክ አለው። ልጡ ወይም የልጡ ውጥ ለትኩሳት፣ ወባ፣ ቁስል ፋሻ፣ የፍላጻ መርዝ፣ ሆድ ቁርጠት፣ የሚያስቀምጥ፣ ኩላሊት በሽታ፣ ሞርሟሪ፣ ጨብጡ፣ እና እብደት ተጠቅሟል።.[2] ከዚህም በላይ፣ ያበጠ ፍስ ውሃ እጢ ለማከም እንደሚችል በትንትና ስለ ተረጋገጠ፣ ውጡ በአውሮጳም ይፈለጋልና ይሼጣል። [3]
ገመሬ ጦጣ (ጎሪላ) በኖረበት አገር ፍሬውን ይወድዳል።
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
- ^ አማረ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
- ^ Stewart, KM (2003). ""The African cherry (Prunus africana): can lessons be learned from an over-exploited medicinal tree?." [Review]". Journal of Ethnopharmacology 89 (1): 3–13. doi:10.1016/j.jep.2003.08.002.
- ^ የጥቁር እንጨት ልጥ ውጥ የፍስ ውሃ እጢ ችግር ማከም ይችላል - ካቅረን cochrane.org