Jump to content

1 ሳባ

ከውክፔዲያ

ንግሰተ ሳባ የነገሰችው በአክሱም አቅራቢያ

በጥንቱ አጠራር ሳባ በምትባለው ከተማ ነበር።

ንግስት ሳባ በአባቷ በአጋቦስ /ተዋስያ/ እግር

ተተክታ ኢትዮጵያን መግዛትና ማስተዳደር

የጀመረችው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1ሺ 13

ጀምሮ ነው።

ንግስት ሳባ የሚለው ሰሟ ሳይሆን የሳባውያን

ንግስት ማለት ነው።የንግስተ ሳባ መጠሪያ ስሟ

በክብረ ነገስት ማክዳ ፣በመፅሀፈ ነገስት

ቀዳማዊና ካልዕ፣ በዜና መዋዕል ንግስተ ሳባ

፣በወንጌል ንግስተ አዜብ ትባላለች።

በዚያ ዘመን የኢትዮጵያ ወሰን ወይም የንግሰተ

ሳባ ግዛት ስፋቱ በምስራቅ እስከ ማዳካጋስካር ፣

እስከ ፋርስ ባህር ፣ በምዕራብ እስከ ኑቢያ ፣

እስከ ምስር /ግብፅ/ ጠረፍ፣ በደቡብ እስከ

ኒያንዛ የቪክቶሪያ ባህር ድረስ ነው ይባላል።በእሷ

ዘመን በኢትዮጵያ የአረብ የግብፅ ፣ የህንድ

የእየሩሳሌም ሰዎች የዘመኑን ሸቀጣ ሸቀጥ ፣

ልብስ፣ሽቶ፣እጣን፣ወርቅና ሌሎች አስፈላጊ

ሸቀጦችን ይነግዱ ነበር።በዚህ ዘመን ደግሞ

በእየሩሳሌም የነገስው የዳዊት ልጅ ሰለሞን

ነበር።

ንግስተ ሳባ በኢትዮጵያ ሰለሞን በእስራኤል

ነግሰው በነበረበት ዘመን ታምሪን የሚባል ነጋዴከ

ኢትዮጵያ ወደ እየሩሳሌም እየተመላለሰ ይነግድ

ነበር።እርሱም ለንጉስ ሰለሞን የሚሆኑ ጥሩጥሩ

እቃዎችን ከኢትዮጵያ ገዝቶ ወስዶ ለሰለሞን

ካስረከበ በዋላ ፣ ሲመለስ የሰለሞንን የቤተ

መንግስት ስነ ስርአትና ጥበቡንም፣ክብሩንም

ሁሉ ለንግሰተ ሳባ ነገራት። በታምሪን አማካኝነት

የተጀመረውም ግኑኝነት እየቀጠለ ሔደ።በዚህ

ነጋዴ አማካኝነትም በሁለቱ ነገስታቶች ሀገር

የማይገኙ እቃዎችን በስጦታ መልክ ይላላኩ

ጀመር ።

ንግስት ሳባ የንጉስ ሰለሞንን ጥበብ የቤተ

መንግስቱንና የስርአቱን ህግና አደረጃጀትበደንብ

ከሚያውቀው ከታምሪን አንደበት ብዙ ጊዜ

እየጠየቀች ከሰማች በዋላ በመጨረሻ በጆሮዋ

የሰማችውን በአይኗ ለማረጋገጥ በብዙ

ወታደሮቿና ደንገጡሮቿ ታጅባ ለሰለሞን

የምታበረክተውን ልዩ ልዩ ስጦታ አሰጪና

በነጋዴው መሪነት ወደ እየሩሳሌም ተጓዘች።

በደረሰችም ጊዜ ንጉስ ሰለሞን በታላቅ ክብርና

በደስታ ተቀበላት።እሷም ከኢትዮጵያ ይዛለት

የሄደችውን የከበረ እንቁና ወርቅ፣ሽቶና ሌሎች

ስጦታዎችን አበረከተችለት።

ንጉስ ሰለሞንም ስጦታውን በክብር ተቀብሎ ልዩ

ማረፊያ ቦታ መርጦ ለሷና ለአጃቢዎቿ

አዘጋጀላቸው።በየቀኑም በእርሱ ትእዛዝ በሬ፣

በግና ፍየልእንዲሁም መጠጥ ለአጃቢዎቿም

ለራሷም እንደ ደንቡ ሲያቀርብላቸው ቆይቶ፣ አንድ

ቀን ንጉስ ሰለሞን ለንግስተ ሳባ ክብር ትልቅ

ግብር/ግባዣ/ አዘጋጅቶ ጠራት።

ከዚህ ግብዣ ቀደም ብሎም ቤተ መንግስቱንና

ቤተመቅደሱን ሲያስጎበኛት ነበረ።በዚህ እለት

ደግሞ ስለ እርሷ ክብር በተዘጋጀው ግብዣ

የአሰራሩን አይነት ፣ የመሳፍንቱንና የመኳንንቱን

አገባብና አቀማመጥ ለማሳየት በራሱ ዙፋን

አቅራቢያ ለእርሷ ልዩ ዙፋን አዘጋጅቶ ዙፋኑንም

እሷ ከውስጥ ሆና ማናቸውንም ነገር ለማየት

እንድትችል ከውጭ በኩል ግን እሷን ማንም

እንዳያያት ተደርጎ በተሰራ መስታወት መሰል ነገር

አስጋርዶ አስቀመጣት። በዚህ ባማረ ዙፋን

ተቀምጣ የመሳፍንቱን ፣ የመኳንንቱን፣የወታደሩን

አገባብና አቀማመጥ፣ በየክፍሉ የሚያገለግሉትን

የወይን ጠጅ አሳላፊዎችና ሰራተኞች አለባበስና

፣የስራቸውን ቅልጥፍና እየተመለከተች ተደነቀች።

ግብዣው ሲጠናቀቅም ንጉስ ሰለሞን ንግሰተ

ሳባን ሊያነጋግራት እርሷ ወዳለችበት ዙፋን

አመራ። እርሷም : "የጥበብህንና የስራህን ነገር

እዚህ ሆኜ በአይኔ ተመለከትኩት፣ በሀገሬ ሳለው

ከሰማውት እጅግ ይበልጣል " በማለት

አድናቆቷን ገለፀች።

ከዚያም ወደተዘጋጀላት ቦታ ለመሔድ

ስትጠይቀው "መሽቷልና እዚህ እደሪ" አላት።

በዚህ ጊዜ ንጉስ ሰለሞን ንግስት ሳባን

ተገናኝቷት አደረ፣ እናም ፀነሰች። በዚህ ጊዜ

ንግስት ሳባ " ልጅህ መሆኑን የምትረዳበት

ምልክት ስጠኝ " በማለት ከሰለሞን የጣቱን

ቀለበት ተቀብላ በቶሎ ወደ ሀገሯ ተመለሰች።

ንግስት ሳባ ከነአጃቢዎቿ ወደ ሀገሯ ስትመለስ

የኤርትራን ባህር ተሻግራ በሀማሴን አውራጃ

ማይበላ ከተባለው ቦታ/ሀገር/ ስትደርስ ወንድ

ልጅ ወለደች።

ንግሰተ ሳባ የወለደችውንም ልጅ ስሙን እብነ

መለክ የሚል ስም አወጣችለት። ትርጉሙም

የንጉስ ወይም የገዢ ልጅ ማለት ነው።እብነ

ሀኪምም ተብሏል። ይህም የብልህ ልጅ ማለት

ነው።

1ኛውም 2ኛውም የስም ስያሜ የጥንቱ

የሳባውያን አነጋገር ሲሆን ፣ታሪኩ የሰፈረበት

ክብረ ነገስት በሳባውያን ቋንቋ ተፅፎ ስለነበረ

በዋላ ላይ እነ ንቡረእድ ወደ ግእዝ ሲተረጉሙት

የአረብኛውን ስም እንዳለ ወስደውት

እንደተረጎሙት ይነገራል።

ምኒሊክም አድጎ 20 አመት እንደሞላው "አባቴ

ማነው ንገሪኝ" ብሎ እናቱን ሲጠይቅ እርሷም

"የእየሩሳሌሙ ንጉስ ሰለሞን ነው" ብላ

ነገረችው። አባቱን ሰለሞንን ለመጎብኘት የእናቱን

ፈቃድ ጠይቆ ወደ እየሩሳሌም ሔደ።

አባቱ ንጉስ ሰለሞን ልጁን ባየው ጊዜ ስሞ

ባረከው። ምኒሊክ ለ3 አመታት ያክል

በእየሩሳሌም የኦሪት ህግ፣ የመንግስት

አስተዳደር በእብራስጥ ቋንቋ ተምሮ ሲጨርስ

ወደ እናቱ ወደ ንግስት ሳባ ተመለሰ። ሲመለሱም

ንጉስ ሰለሞን ልብሰ መንግስት አልብሶ ከ12ቱ

ነገደ እስራኤል 12ሺ የእብራዊ የበኩር ወንድ

ልጆች /ከእያንዳንዱ ነገድ 1ሺ 1ሺ ማለት ነው።

/ የዳዊትን ልጅ ወንድሙን ጨምሮ ብልሆችንና

አዋቂዎችን መርጦ ፣ ከተማሩትም ካህናት

እንዲሁም ከመሳፍንቱ ልጆች 22 ታላላቅ

ሹማምንት ጋር የኢትዮጵያ ንጉሰነገስት ይሆን

ዘንድ ልብሰ መንግስቱን አሰፍቶ ፣ ቅብዓ ሜሮንን

በሊቀ ካህናቱ በሳዶቅ አስቀብቶ፣ ከክርስቶስ

ልደት በፊት በ982 ወደ ኢትዮጵያ ሸኘው።

ንግስተ ሳባ ልጇ ምኒሊክ ከእየሩሳሌም ሲመለስ

በታላቅ ክብር ሰልፍ አድርጋ ተቀበለችው።

ምኒሊክና ሰዎቹ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ አዛርያስ

በሚባለው ሊቀካህን አማካኝነትበልኡል

እግዛብሔር ጣቶች ተቀርፆ ለሙሴ የተሰጠው

እውነተኛ ፅላት ወደ ኢትዮጵያ አብሮ መጣ። ፅላቱ

በአሁን ሰዓት በአክሱም ፅዮን ቤተክርስቲያን

አምላክ በመረጣቸው ሰዎች እየተጠበቀ

እንደሚገኝ ነው የሚታወቀው።

ከዚያም ንግሰተ ሳባ ምኒሊክን ተቀብላ በሕይወት

እያለች በኢትዮጵያ አነገሰችው።ንግስተ ሳባ

በኢትዮጵያ ለመንገሷ ከታላቁ መፅሀፍ ቅዱስ

ጀምሮ በሁሉም ታሪካዊ መፅሀፎች ውስጥ

የተረጋገጠ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ ገናና ንግስትና

በጥበብ የተሞላች እንደነበረችም ይታወቃል።

ቀዳሚው
ሆርካም
ኩሽ ንጉሥ ተከታይ
ሶፋሪድ