7ኛ
ወራሪው የፋሽስት ጣልያን ሰራዊት በኢትዮጵያውያን ጀግኖች የካቲት 23 /1888 ዓ.ም ተደመሰሰ የካቲት ሃያ ሦስት (23) ቀን ሺህ ስምንት መቶ ሰማኒያ ስምንት (1888) ዓመተምህረት መላ የኢትዮጵያ ህዝብና ጀግኖች አርበኞች በአንድነት የኢጣሊያንን ቅኝ ገዢ ወራሪ ጦር ዓድዋ ላይ ድል ያደረጉበት ዕለት ነበር‼ ዝክረ_ታሪክ ከአንድ መቶ ሃያ ዘጠኝ (129) ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት ታሪክን የኋሊት!! በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ ዳግማዊ አጼ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ አገሩን በሙሉ እስከ ሶሎዳ በደንብ በሚያሳያው በጥንታዊው የአባ ገሪማ ገዳም ከፍታ ላይ ሰፍረው ነበር፡፡ ጦርነቱ እንደተጀመረ የመሳሪያው ድምጽ በገደል ማሚቱ እየተቀባበለ እስከ አሥራ ሰባት (17) ማይል ዘልቆ ይሰማል። እስከ ጥዋቱ አራት (4) እና አምሥት (5) ስዓት ድረስም ሁሉም የኢትዮጵያ ጦር ስራ ላይ ነበር፡፡ ንጋት አስራ ሁለት (12) ሰዓት አካባቢ የጄኔራል አልበርቶኒ ጦር ከመሸገበት የሰማዕታ ኮረብታ ማጥቃት ጀመረ፡፡ ጦርነቱ ሲጀመር የጄኔራል አሪሞንዲ ጦር በተመደቡበት ቦታ ባለመገኘቱ ጄኔራል አልበርቶኒ ወዲያው ተጨማሪ ጦር እንዲላክለት ወደ ጣሊያን ሠራዊት ዋና አዛዥ ጄኔራል ባራቴሪ መልእክተኛ ላከ፡፡ መጀመሪያ ላይ ጦርነቱ የመድፍ ፍልሚያ ነበር የሚመስለው፡፡ የጄኔራል አልበረቶኒ ጦር የኢትዮጵያ ሠራዊት የውጊያ ትእዛዝ በመቀበል ቦታ ቦታውን እስኪይዝ በተራራው ላይ መድፎችን እያከታተለ ይተኩስ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፈጣኖቹ የኢትዮጵያ ተኳሾች ወደ ስራ እንደገቡ በፍጥነት የመድፎቹን አፍ አዘጉት፡፡ በግራ በኩል የንጉሥ ተክለ ኃይማኖት ጦርና በመሀል የንጉሥ ምኒልክ ጦር እንዲሁም በቀኝ በኩል የራስ ሚካዔልና የራስ መንገሻ ጦር የጄኔራል አልበርቶኒን ጦር ይዞታ እየተቀባበሉ መፈናፈኛ አሳጥተው ቀጠቀጡት፡፡ ኢትዮጵያውያን የገሪማ ተራራን ዝቅተኛ ክፍሎች በመያዝ በጣሊያኖች ላይ ጥይታቸውን ያዘንቡት ጀመር የጄኔራል አል
አልበርቶኒን ጦር ከበባ ውስጥ ከተቱት፡፡ በመቀጠልም ወደ ጥሻው በመግባት ወደ ሸለቆው የሚወስደውን መተላለፊያ መንገድ ሰብረው ያዙት፡፡ ከዚህ በመቀጠል አልሞ ተኳሽ ኢትዮጵያውያን ዋናው የተራራው አናት ላይ በመውጣት የጄኔራል አልበርቶኒ ጦር ላይ ጥይታቸውን ቁልቁል ማዝነብ ጀመሩ፡፡ ለአምሥት (5) ሰዓታት ያህል እስከ ቀኑ አምሥት (5) ሰዓት የተዋጋው የኢጣሊያ ሰራዊት ግራ ክንፍ ይህንን ምት በጭራሽ መቋቋም ባለመቻሉ የተረፉት እጃቸውን ለመስጠት ተገደዱ፡፡ በዚህ ግንባር የነበረው የኢትዮጵያ ሰራዊት ግንባሩን ካጸዳ በኋላ በራዮ ተራራ ላይ ከብርጋዲየር አሪሞንዲና ኤሌና ጋር እየተዋደቀ ላለው የወገን ጦር ድጋፍ ለመስጠት ወደዛው አመራ፡፡ የራስ መኮንን፣ የራስ መንገሻ፣ የራስ ወሌና የዋግ ሹም ጓንጉል ጦር ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ የኢጣሊያን ጦር የመሃል ግንባር በራዮ በኩል ይቀጠቅጡት ጀመረ፡፡ ከጄኔራል ዲቦርሚዳ ጋር በሌላ ግንባር እየተዋደቀ ያለውን የራስ አሉላ ጦር ለማገዝ ወደዛው የገሰገሰው የራስ ሚካዔል የኦሮሞ ፈረሰኞች ሰራዊትም በቦታው ደርሶ የዲቦርሚዳን ብርጌድ ወደ ፊት እንዳይገፋ በማገድ ያጠቃው ጀመር፡፡ የኢትዮጵያ ሰራዊት በራዮና በኪዳነምህረት የሰፈረውን የኢጣሊያ ጦር በሁሉም አቅጣጫ ከበባ ውስጥ በመክተት ማጥቃት ጀመረ፡፡ የኢትዮጵያ ወታደሮች እንደ አምበጣ መንጋ በብዛት ወደ ተራራው ጫፍ በመውጣት ወደ ኢንቲቾ፣ አካለ ጉዛይና አዲግራት የሚወስድውን የመምሳን መተላለፊያ መንገድ ዘጉት፡፡ ጄኔራል አሪሞንዲም ከምርጥ ብርጌዶቹ ጋር በመሆን የሚችለውን ሁሉ ካደረገ በኋላ በመጨረሻ በተረፉት የብርጌዱ አባላት ፊት ወደቀ፡፡ የዳግማዊ ምኒልክ ጦር የጣሊያንን ሰራዊት በአስተማማኝ ሁኔታ ከማሸነፉም በተጨማሪ ወደ አራት ሺህ (4) የሚጠጉትን ማርኳል፡፡ ከምርኮኞቹ መካከልም አንድ ጄኔራልና በርካታ የጦር መኮንኖች ይገኙበታል፡፡ ወደ ስልሳ አምሥት (65) የሚጠጉት የኢጣሊያ መድፎች ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን አርበኞች ተማርከዋል፡፡ ከሞት የተረፈው አብዛኛው የኢጣሊያ ሰራዊት መሳሪያውን እየጣለ በመፈርጠጡ ወደ አስራ አንድ ሺህ (11) የሚጠጋ ጠመንጃም በኢትዮጵያውያኑ አርበኞች እጅ ገብተዋል፡፡ በጦርነቱ ከአምሥት እስከ ስድስት ሺህ (5-6) የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን አርበኞች በጀግንነት የተሰዉ ሲሆን ወደ ስምንት ሺህ (8) የሚጠጉ ደግሞ ቆስለዋል፡፡ አብዛኞቹ ቁስለኞች አድዋን፣ አክሱምን፣ መቀሌን፣ አቢ አዲንና አጎራባች አካባቢዎችን ሞልተዋቸው ነበር፡፡ የኋላው_ከሌለ_የለም_ የፊቱ‼ ይህ_የኛ_ የኢትዮጵያውያን_ታሪክ_ ነው‼
ምንጭ፦ British War Correspondent Augustus Wylde, Modern Abyssinia, PP 205-210, 212, Published in London in 1901
- ቪቫ_ምኒሊክ‼ *ምኒሊክ_ዛሬም_ንጉስ_
ነው‼ 23/06/2017 ዓ.ም
| ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |