Jump to content

8ኛ

ከውክፔዲያ

ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው የአገው የፈረሰኞች በአል የአመቱ አንባሳደርነትህን ከአርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ መረከባቸውንና የእንኳን አድረሳቹህ መልክት አስተላለፉ። የተከበራችሁ በሁሉም የሃገራችን ክፍል እና ከአገር ውጭ የምትኖሩ የፋኖ ደጋፊዎች እና የፋኖ አባላት እንዲሁም የፋኖ አመራሮች እና ለመላው የአገው ህዝብ እንኳን ለ85ኛው የአገው ፈረሰኞች ባህል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ታሪካዊ ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ዳራ ያለው በየዓመቱ ጥር 23 የሚከበረው የአገው ፈረሰኞች ማህበር ክብረ በዓል እና የፈረስ ፌስቲቫል ዘንድሮ ለ85ኛ ጊዜ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል ።የአገው ፈረሰኞች የነፃነት ተጋድሎ ያስመስከሩ እና በአድዋ ጦርነትም ጀግንነታቸውን ያሳዩ መሆናቸው በታሪክ የተመዘገበ ነው።ፈረስ ለአገው ህዝብ ሀገሩን ከጠላት ለመከላከል ለአርበኞች የጀግንነት ክንዶች ናቸው።ከዚህ በተጨማሪም ለመጓጓዣ : ለሰርግ ለሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች፤ ለለቅሶ ስርዓት፣ለእርሻ አገልግሎት በመስጠት ከህዝብ ጋር የተሳሰረ ቁርኝት አለው፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከፍተኛ የቱሪዝም መዳረሻ እየሆነ የመጣው የሰባት ቤት አገው ፈረሰኞች ማህበር የአገው ህዝብ ብሎም የአማራ ህዝብን በማስተዋወቅ እረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው በአሁኑ ወቅት የበዓሉ አድማስ ከአካባቢው ማህበረሰብ አልፎ በሃገር አቀፍ ደረጃ ቦታ የሚሰጠው ነው፡፡ በየዓመቱ በጥር ወር የሚከበረው ይህ ክብረ በዓል የበርካቶች ዓይን ማረፊያ ሆኗል ከሁሉም የሃገሪቱ አካባቢዎች የመጡ ልምድ ያላቸው ጋላቢዎች በጉግስ ሽርጥ እና በሌሎች የውድድር አይነቶች እነዚህን ፈረሶች በመጋለብ ፡በታዳሚው ፊት ልክ በጦርነት ወቅት ፈረሶች እንደነበራቸው ሚና በማስመሰል ትርዒት ያሳያሉ፡፡ በ1932 ዓ.ም በወርሃ ጥር የተመሰረተው የአገው ፈረሰኞች ማህበር የአገው ህዝብን ታሪክ ባህል እና እሴት አክብሮ በሌሎች ዘንድም ይከበር ዘንድ የአበረከተው አስተዋፅኦ ሶስት የትውልድ ቅብብሎሽን ተሸግሮ የአራተኛው ትውልድ ላይ ደርሷል፡፡ 30 አባላትን ይዞ የተመሰረተው የአገው ፈረሰኞች ማህበርበ አሁኑ ወቅት የአባላቱ ቁጥር ከመቶ ሽ በላይ ደርሷል።የአገው ፈረሰኞች ማህበር የአገው ህዝብ ሃገራዊ አንድነቱን በጀግንነቱ የአፀና ለመሆኑ ማሳያ ብቻም ሳይሆን አገውነት ለሃገር ክብር የመዋደቅ ጀግንነትን፤ስለሃገር ሲሉ በልበ ሰፊነት መስዕዋት የሆኑ ጀግኖችን ውለታ አክባሪ መሆኑንም ጭምር በተምሳሌነት በዚህ ባዕል ላይ ይዘከርበታል።አሁንም ጀግንነቱን በፋኖ ዘመን አሳይቶናል፡፡ ጥር 23/2017ዓ.ም ለሚከበረው የአገው ፈረሰኞች ባዕል የእመቱ የክብር አንባሳደር ሆኘ እንባሳደርነቱን ከአርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ ስረከብ በታላቅ ክብር እና ኩራት ነው የአገው ህዝብ በማንነቱ የማይደራደር ፤የእውቀት፣ የጥበብ፤የፍልስፍና የባዕል፤የሃይማኖት የጀግንነት፤የሃገር ገንቢነት እና ሃገር ወዳድነት ተምሳሌት እንዲሁም የስልጣኔ ባለቤት የሆነ ህዝብ ነው።በዓለም ከላይ ወደታች ስነ ህንፃ ስርቶ ያስረክበ፥ በሃገር ግንባታውም አኩሪ ተሳትፎ ያለው እንደሆነ ታሪክ ይነግረናል ፡፡ በተለይም በያዝነው የህልውና ተጋድሎ ውስጥ ደማቅ ታሪክ እየፃፉ ያለ ጀግና ተዋጊዎችን እና እንቁ የትግሉ አመራሮችን ከማፍራት አልፎ ለህልውና ተጋድሎ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁለንተናዊ አበርክቶውን በመወጣት ላይ ይገኛል።ለዚህም የአማራ ፋኖ በጎጃም የአገው ፈረስኞችን ክብረ ባዕል በየዓመቱ የሚዘክረው ይሆናል።ትግሉ በመላው አማራ በአድስ መንፈስ ይቀጥላል፡፡ በጥንታዊ ኢትዮጵያ ፤አገው ፈረሰኞች በአክሱም መንግስት ዘመን የጦር ሃይሎች አካል ነበሩ አክሱም ከጎረቤት መንግስታት ጋር በሚደረጉ ጦርነት ውስጥ እነዚህ ፈረሰኞች ወሳኝ ሚና ይጫወቱ ነበር።በተለይም በከፍተኛ ሜዳዎች ላይ የሚደረጉ ጦርነቶች ውስጥ የፈረስ ጦር በጣም ውጤታማ እና አገዎችም ውጊያ ይወዱ ነበር። በመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ንጉስ ነገስታት አገው ፈረሰኞችን በማዕበል ላይ በሚደረጉ ጦርነቶች ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ይጠቀሙ ነበር።በዚህ ጊዜ የአገው ሰዎች በጦር ሜዳ ላይ የሚያሳዩት እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ እና ውጤታማነት በታሪክ ውስጥ ተመዝግቧል፡፡ አገው ፈረሰኞች በጦር ሜዳ ላይ የሚያሳዩት የጦር ስልት ከፍተኛ ነበር እነሱ በፍጥነት እና በትንሽ የጦር ሃይል በተቃራኒው ላይ ከፍተኛ ድል ማድረግ ይችሉ ነበር።በተጨማሪም የአገው ፈረሰኞች በተለይም በተራራማ እና አስቸጋሪ ቦታዎች ላይ ጦርነት ለማድረግ የተካኑ ነበሩ። በብዙ የባህል በዓላት እና በታሪካዊ ትውስታዎች ውስጥ የአገው ፈረሰኞች ስም ይገኛል። በአድዋ ጦረነት ' የአምስት ዓመቱ የጣሊያን ጦርነት ከአንድ ሽ በላይ የአገው አርበኞች ሴቶችን ጨምሮ እንደተሳተፉ የሚገልፁ ማስረጃዎች አሉ፡፡ በተለይም በያዝነው የህልውና ተጋድሎ ውስጥ ደማቅ ታሪክ እየፃፉ ያሎ ጀግና ተዋጊዎችን እና እንቁ የትግሉ አመራሮችን ከማፍራት አልፎ ለህልውናው ተጋድሎ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁለንተናዊ አበርክቶውን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡ የአማራ ፋኖ በጎጃም የአገው ፈረሰኞችን ክብረ ባዕል በየዓመቱ የሚዘክረው ይሆናል ትግሉ በመላው አማራ በአድስ መንፈስ ይቀጥላል፡፡ በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ እንኳን አገው ፌሬስታት ስሁታንቲ እንኮ ማህቢሪስ ታምፁናስ፡ የአማራ ፋኖ በጎጃም ም/ ሰብሳቢ እና ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ደለለ 23/05/2017 ዓ.ም