ሊብረቪል

ከውክፔዲያ

ሊብረቪል (Libreville) የጋቦን ዋና ከተማ ነው።

የሊብረቪል መዘጋጃ

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 661,600 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 00°30′ ሰሜን ኬክሮስ እና 09°25′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ፈረንሳይ1831 ዓ.ም. ዙሪያውን ካገኙ በፊት፣ የረጅም ጊዜ ኗሪዎቹ የምፖንግዌ ጎሣ ነበሩ። ከተማው 'ጋቦን' ተብሎ የንግድ ጣቢያ እንዲሆን በ1835 ዓ.ም. ተሠራ። ከባርነት ነጻ የወጡ ጥቁሮች በዚያ ስለ ሰፈሩ ከ1840 ጀምሮ ፍሪታውንን በመምሰል ቦታው 'ሊብረቪል' ('ነጻ ከተማ' በፈረንሳይኛ) ተሰየመ።