ከ«እስልምና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
roboto aldono de: ext:Islam
roboto aldono de: xal:Лал шаҗн
መስመር፡ 254፦ መስመር፡ 254፦
[[wo:Lislaam]]
[[wo:Lislaam]]
[[wuu:回教]]
[[wuu:回教]]
[[xal:Лал шаҗн]]
[[yi:איסלאם]]
[[yi:איסלאם]]
[[yo:Islam]]
[[yo:Islam]]

እትም በ14:24, 27 ኖቬምበር 2009

የእስልምና መጠን በየሃገሩ፦ ቀይ (ሺዓ) አረንጓዴ (ሱኒ)

እስልምና (አረብኛኢስላም) ማለት ከአባታችን አደም (አዳም) ጀምሮ እስከ ነብዩሏህ ኑህ(ኖህ) ያሉት ሁሉም ነብያት ሃይማኖት ሲሆን ነቢዩ ሙሐመድ (የአላህ እዝነት እና ሰላም ይስፈንባቸው እና) እንደመጨረሻ ነብይነታቸው ያስተማሩት ሃይማኖት የሚታወቅበት መጠሪያ ስም ሲሆን የእምነቱ ተከታዮች ደግሞ ሙስሊም (አማርኛእስላም) በመባል ይታወቃሉ።
ኢስላም የሚለው ጥሬ ቃል ቋንቋ 3 ትርጉሞችን ያዘለ ሆኖ እናገኘዋለን። እነሱም

1ኛ ከግልጽ ወይም ስውር ከሆኑ ጉድለቶች ፍጹም ነጻ የመሆን እና የመጥራት
2ኛ እርቅ እና እርጋታ
3ኛ ሰሚነት እና ቅን ታዛዥነት የሚለውን ትርጉም አዝሎ ይገኛል።(ww.islamhouse.com)

ኢስላም ህጋዊ ትርጉም

ኢስላም ማለት ለፈጣሪ እጅን መስጠት እና በ ትእዛዙ ማደር(ስብሚሽን ቱ ዘ ዊል ኦፍ ጎድ ) ማከት ሲሆን አምልኮትን ሁሉ በብቸኝነት ፍጹም ለአላህ ማድረግ ።ሌሎችን ፍጡራን የስልጣኑ ተጋሪ አለማድረግ ፡ይህን ዩኒቨረስ ብቻውን የፈጠረ /ለፍጡራን ሁሉ ሲሳያቸውን እሱ ብቻውን የሚመግብ /ለስልጣኑ ተጋሪ ወይም እረዳት ተባባሪ የሌለው ሃያል ጌታ መሆኑን ማመን ።ነገ የትንሳኤ ቀን የፍርዱ ቀን ብቸኛ ባለቤት አላህ መሆኑን ማመን። ይህን ይመስላል ብለን የምንመስልበት አምሳያ የሌለው ሃያል አምላክ አላህ በመባል ይታወቃል።

 ኢስላም ማለት  ለአላህ በመመሪያው በማደር ለትእዛዞቹ መንበርከክ ፡ እምነትን እና ልቦናን ለአላህ ፍጹም ማድረግ እና ከአላህ ዘንድ የመጡ መመሪያዎችን በፍጹምነት ማመን ነው።
  • አንድ ሰው ሙስሊም ነው ሊባል የሚቻለው የዚህ ግዙፍ አለም ሆነ ሌላ አለ የሚባለው አለም እና በውስጧ ያሉት ነገሮች ሁሉ ፈጣሪ ተቆጣጣሪ አስተናባሪ ብቸኛ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን እና ነቢዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) የመጨረሻው መላክተኛ ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በአጭር አማርኛ :- በእውነት የሚያመልኩት አምላክ ከአላህ በስተቀር የለም። ነብዩ ሙሐመድም ባሪያው እና መላክተኛው ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በአረብኛ «ላኢላሃ-ኢለሏህ ሙሃመድ ረሱሉሏህ» በመባል ይታወቃል።

ኢስላም እጅግ በጣም ቀላል እና ውስብስብስ ያልሆኑ መሰረታዊ የእምነት መርሆዎችን ያዘለ በመሆኑ እና ከሰው ልጅ መሰረታዊ እና ተፈጥሯዊ ፍላጎት ጋር የሚመጣጠን ህግ እና ደንብ ያዘለ በመሆኑ እነሆ በዓለም ላይ ተከታዮቹ ከ1.2 ቢሊዮን በላይ ሆነው ይገኛሉ።

ሱና ማለት የነብዩ ሙሐመድ ንግግር እና ስራ/ስሩ ብለው ያዘዙት እና ሲሰራ እያዩ በዝምታያለፉት (አትስሩ ብለው ያልከለከሉት) በአጠቃላይ በህይወታቸው የሰሩት ስራ እና እንዲሰራ ያዘዙት ሁሉ ሱና ይባላል።

ማንኛውም ሙስሊም ኢስላምን የሚተገብረው ከነብዩ ሙሐመድ በተማረው መሰረት ብቻ ነው።ኢስላም ሙሉ እምነት ስለሆነ ከጊዜ ብዛት አነሰ ተብሎ የሚጨመርበት ወይም በዝቷል ተብሎ የሚቀነስለት ነገር የለውም።

      • ሙስሊሞች ለማንኛውም ቦታ እና ጊዜ/ዘመን /የሚያገለገል ቁርዓን እና ሃዲስ የሚባል መመሪያ አላቸው።ይህን መመሪያም ነብዩ ሙሐመድ ባስተማሯቸው ሱና መሰረት ይተገብሩታል።

እነዚህ የ እምነቱን ድንጋጌዎች የሚያስተምሩት መመሪያዎች ቁርአን እና ሃዲስ ሲሆኑ ቁርአን ማለት በ መልአኩ ጅብሪል አማካኝነት ወደ መሃመድ በወህይ የተወረደ የአላህ ቃል ማለት ነው። ሃዲስ ማለት ደግሞ ነብዩ ሙሐመድ ንግግሮች ናቸው ።

ኢስላም የነብያት ሁሉ ሃይማኖት መሆኑን ሙስሊሞች ጠንቅቀው ያምናሉ። ከአባታችን አደም (አዳም) ጀምሮ እነ ነብዩሏህ ኖህ ነብዩ ሙሳ ነብዩሏህ ኢሳ ...እንዲሁም ሌሎች ነብያት ሙስሊሞች ነበሩ። እና ኢስላም ከጥንትም ከጠዋትም የሰው ልጅ የተፈጥሮ እምነት ነውማለት ነው። ይህ በመካ አሁን ያለው እና ካዕባ በመባል የሚታወቀው ግንብ በነብዩ ኢብራሂም አብርሃምእና ልጃቸው ዒስማኤል የተሰራ በመሆኑ ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች እንኳ የአብርሃም ግንብ በማለት ይጠሩታል።

ይህ የሚያመለክተው ነገር ቢኖር የሰው ልጆች ከእምነት ጎዳና እያፈነገጡ ጣኦት ማምለክ በሚጀምሩበት ወቅት ፈጣሪ በየጊዜው መልእክተኛ እየላከ ይገስጻቸው እንደነበር እና ከነብዩ ኢሳ (ኢየሱስ) በኋላ ለመጨረሻ ጊዜ ነብዩ ሙሐመድ መላካቸውን ኢስላም ያስተምራል። ከኢሳ በኋላ ነብይ እንደሚላክ በመጽሃፍ ቅዱስ ሳይቀር እንደተነገረ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ከማስረዳታቸውም በተጨማሪ ቁርአንም ቢሆን እንዴት ሰዎች ከአረቡ አለም መልእክተኛ ይላካል? ለምን ከእስራኤል ወገን እንደጥንቱ አይላክምም በማለት አይሁዶች እውነታውን ካወቁ በኋላ በምቀኝንነት ኢስላምን አንቀበልም ማለታቸው እና በነብዩ ሙሀመድ መልእክት ማስተባበላቸውን በማያሻማ ሁኔታ ግልጽ አድርጎ አስቀምጦታል።

  • ኢስላም ለመረዳትም ሆነ ለማስረዳት እጅግ ቀላል ነው። ከሌሎች እምነቶችም ልዩ የሚያደርገው የዚህን ዓለም ፈጣሪ አንድ ብቻ መሆኑን እና ሊመለክም የሚገባው ዕሱ ብቻ መሆኑን ማስተማሩ ሲሆን ለእርሱ ረዳትም ሆነ የስልጣን ተካፋይ ፈጽሞ የሌለው የሚፈልገውን ሰሪ ብቻውን ቀሪ እንደሆነ ኢስላም ጠንቅቆ ያስተምራል። እናም በአንድ ሃገር ሁለት መንግስት እንደማይኖር ሁሉ ይህ ዩኒቨርስም አንድ ፈጣሪ ብቻ ነው ያለው በማለት ኢስላም ሌሎች እንደ ፈጣሪ ተደርገው እንዳይመለኩ ያስጠነቅቃል። ምክንያቱም ምን ነገር ማድረግ አቅሙም ሆነ ብልሃቱ የላቸውም እና ነው። ከአላህ ሌላ ያለን ፍጡርም ይሁን ማንኛውም አይነት ነገር ማምለክ በኢስላም ታላቅ ወንጀል ነው።

ኢማን (የልብ ስራ) 6 መሰረታዊ ነግሮችን አጠቃልሎ ይዟል።

1ኛ በአላህ ማመን
2ኛ መላእክት እንዳሉት ማመን
3ኛ በኪታቡ (በመጽሃፎች ማመን)
4ኛ በሩሱሎች ማመን
5ኛ በመጨረሻው ቀን የፍርድ ቀን (ሞቶ መነሳት) እንዳለ ማመን
6ኛ በቀደር ማመንን

የሚሉት ሲሆኑ ሰፋ ያለ ትንታኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ናቸው። የኢስላም መሰረታዊ ነገሮች 5 ሲሆኑ

1ኛ አላህ አንድ ነው ሙሀመድ መላክተኛ ነው ብሎ ማመን
2ኛ ሰላት መስገድ
3ኝ ዘካ ማውጣት
4ና ጾም መጾም
5ኛ ሃጅ ማድረግ ናቸው።

ከላይ የኢማን መሰረቶች 6 ናቸው ብለናል በመጠኑም ቢሆን በዝርዝር ለማየት እንሞክር 1ኛ / በአላህ ማመን ማለት ሲዘረዘር ይህን ዓለም ብቻውን የፈጠረ፡ብቻውን የሚያስተዳድር እና የሚቆጣጠር፡ለፍጡራን ሲሳይ የሚለግስ፡ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን ማለት ነው። ይህ አለም ካለ ፈጣሪ አልተገኘም። የሰው ልጅም ካለ አላማ ወደዚህ ምድር አልመጣም።ያመጣው አንድ ፈጣሪ አለው።የመጣውም ለአላማ ነው። የመፈጠራችን አላማም ፈጣሪያችንን ለማምለክ ነው። ይህን አለም መጥኖ አስተካክሎ የፈጠረው ፡ሰማይን ካለ ምሰሶ ያቆመው ጸሃይ እና ጨረቃ እንዲሁም ለሊት እና ቀን ሌሎችንም ፕላኔቶች መስመራቸውን ይዘው /ጠብቀው እንዲጓዙ የሚያደርግ አምላክ ፈጣሪ አስተናባሪ ተቆጣጣሪ/አላህ ነው ብሎ ማመን አንዱ የኢማን መሰረት ነው። ከማንኛውም አይነት እንከን እና ጉድለት የጠራ/በሰው ልጅ ላይ የሚታዩ የድክመት ምልክቶች ፍጹም የማይታዩበት ፡የማይበላ እና የማይጠጣ የማይወልድ የማይወለድ ፍጹም የ እሱም ቢጤም ሆነ አምሳያ ስለሌለው ይህን ይመስላል ብለን ልንመስለው የማንችል ሃያሉ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን ።

      • እሱ ለምን ሰራህ ተብሎ ሊጠየቅ የማይችል እሱ ግን የፈለገውን የሚሰራ እና የሚጠይቅ /የሚምር የሚቀጣ/የሚፈጥር የሚገድል/የሚያስታምም የሚያድን/ የፈለገውን ሰሪ ብቻውን ቀሪ የፍርዱ ቀን ባለቤት አላህ ነው ብሎ ማመን አስፈላጊ እና የግድ ነው።

2ኛ በመላእክት(በመላኢኮች ማመን) ከብርሃን የተፈጠሩ የማይበሉ የማይጠጡ ከተፈጠሩ ጀምሮ የፈጣሪን ትእዛዝ ብቻ በመተግበር ላይ የሚዘወትሩ ፡መላእክት አሉት ብሎ ማመን የግድ ሲሆን ከነዚህ መላእክት ዋናዋናዎች ጂብሪል ሜካኤል ኤስራፊል ...የመሳሰሉት ይገኙበታል። እነዚህ መላእክት ከራሳቸው ምንም ማድረግ የማይችሉ የማይጠቅሙ እና የማይጎዱ በመሆናቸው አምልኮ ለነሱ ተገቢ አይደለም።እነሱ ፈጣሪያቸውን ሌት ከቀን በቅንንነት ያመልካሉ ፡አመጸኞች አይደሉም።ተግባራቸው የተለያየ ነው።በጣም ትልቅ ፍጥረት ናቸው።ጅብሪል የሚባለው መላእክት 700 ክንፎች ሲኖሩት አንዱ ክንፍ ብቻ ሲዘረጋ ከጀምበር መግቢያ እስከ መውጫ ይደርሳል።ይህ የሚያሳየው የ እነዚህ ፈጣሪ ምን ያህል ታላቅ መሆኑን ነው አሏሁ አክበር!!! 3ኛ በኪታቦች ማመን አለት ከላህ ዘንድ ለተለያዩ ነብያት እንደወቅቱ ሁኔኤታ የተላቁ ኢንጂል ተውራት ዘቡር እና ሌሎችም ለሙሳ እና ለኢብራሂም የተሰጡ ጽሁፉች እና ቁርአን ከአላህ ዘንድ የወረዱ ናቸው ብሎ ማመን የግድ ሲሆን። በመመሪያነት ግን ከቁ አን ውጭ በአሁኑ ሰአት አያገለግሉም።ምክንያቱም ቁር አን ሁሉንም ህግ አጠቃልሎ ለሰው ልጅ በሙሉ የመጨረሻ መመሪያ ሆኖ ነው የወረደ።ከቁር አን ውጭ ያሉት መጽሃፍት በሰው ልጆች ተበርዘዋል ተከልሰዋል።ቁር አን ግን እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ በተአምርነቱ ሳይበረዝ ሳይከለስ እንዲቆይ ፈጣሪ እንደሚጠብቀው ቃል ገብቶለታል። 4ኛ በሩሱሎች ማመን ማለት አላህ ይህን ዓለም ከፈጠረ ጀምሮ እስከ ነብዩ ሙሐመድ ድረስ ሰዎች ቀጥተኛውን የኢስላም መንገድ ይዘው ይጓዙ ዘንድ ነብያትን መረክተኛ ድርጎ ልኳል ።ስለዚህ በሩሱሎች (ማለት መላክተኛ ማለት ነው)በመላካቸው ማመን 5ኛ በመጨረሻው ቀን ማመን ማለት ይህ አለም መጨረሻ እንዳለው እና በዚህ ምድር የሰራውን ስራ ተገምግሞ እና ታስቦ መልካም ሰሪው በጀነት የሚመነዳበት በጥፎ ሰሪው በገሃነም የሚቀጣበት የሂሳብ እርና የፍርድ ቀን አለ ብሎ ማመን ማለት ነው። ይህ የፍርድ ቀን የትንሳኤ ቀን ማለት ሲሆን ልክ ከ እንቅልፋችን እንደምንነሳው ሁሉ ሁሉም ሰው ከመቃብሩ እየተነሳ ወደ ፍርዱ ቀን ሜዳ የሚሰበሰብበት ቀን መኖሩን ማመን። ለምሳሌ እንቅልፍን ብንወስድ የሞት ታናሽ ወንድም ማለት ነው ሞቶ መነሳት እንዳለ ለሚያስተባብሉ ይህች እንቅልፍ ትንሽ ምሳሌኤ ልትሆን ትችላለች። 6ኛ በቀዷ በቀደር ማመን ማለት። ጥሩም ይሆን መጥፎ ነገር ተጽፎ እና ተወስኖ ያለፈ መሆኑን አምኖ በጸጋ መቀበል ማለት ነው።አንድ ሰው ወደዚህ ምድር ከመምጣቱ በፊት በምድራዊ ህይወቱ ምን እንደሚያጋጥመው ተወስኖ ተጽፎ አልፏል።ስለዚህ ያልተጻፈበትር አያገኘውም ያልተጻፈለትንም አያገኝም። እሱ ግን እጣ ፈንታው ምን እንደሆነ ስለማያያውቅ ፈጣሪ ያዘዘውን ብቻ ትእዛዝ መፈጸም ነው ያለበት። አላህ የምንፈልገውን እንድንሰራ ጫና ሳያደርግ ምርጫ ሰጥቶናል።ዛፍ ወደ ተቆረጠበት እንደሚያዘነብል ሁሉ ሰዎችም መልካም ከሰሩ መልካም መጥፎ ከሰሩ ደግሞ ያንኑ ይመነዳሉ(አላህ የበለጠ ያውቃል)

የኢስላም መሰረቶች በ 5 ይከፈላሉ ብለናል 1ኛ አላህ አንድ ነው ሙሐመድ መላክተኛ ነው ብሎ ማመን ማለት ነው፡፤ይህ የ እምነቱ የማዕዘን ድንጋይ ወይም ቁልፍ ነው ማለት ይቻላል፡፤አንድን ሙስሊም ሙስሊም ያሰኘው እና ከሙስሊሞች ቤተሰብ እንዲቀላቀል የሚያደርገው ወሳኝ ቃል በአረብኛ ላኢላሃ ኢለሏህ ሙሐመድ ረሱሉሏህ የሚባለው በአማርኛ ደግሞ በ እውነት የሚያመልኩት ጌታ ከላህ በስተቀር የለም የሚለው ቃል ነው። 2ኛው ሰላት መስገድ ሲሆን የትንሳኤ ቀን ለመጀምሪያ ጊዜ የሰው ልጅ ሂሳቡ የሚጀምረው ከሰላት ነ፡፡ ሰላቱ የጎደለ ሰው ሌኤላው ስራው አይሞላለትም።ለዚህም ነው ሙስሊም ብነሆነው እና ባልሆነው ሰው መካከል ያለው ልዩነት ሰላት መስገድ ነው በማለት ነብዩ ሙሀመድ ያስተማሩት። ሰላት በቀን 5 ጊዜኤ ሰአት ተወስኖለት የሚተገበር የአምልኮት አይነት ሲሆን እነሱም ፈጅር (ሱብህ) ዝሁር አስር መግሪብ ኢሻ በመባል ይታወቃሉ ።እነዚህ በማንኛውም አካለመተን በደረሰ እና ዐምሮው ጤነኛ በሆነ ሙስሊም ላይ የግዴታ ሰላቶች ናቸው ።ሌሎች ደግሞ ዱሃ እና የሌሊት ሰላት የሚባሉ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረቱ ታላቅ ምንዳ የሚያስገኙ የሰላት አይነቶች አሉ። የፈጅር ሰላት ሁለት ረከዓ ሲሆን የሚሰገደው ከፈርድ ሰላት በፊት(ከዋናው የፈጅር ሰላት በፊት 2 ረከዓ ሱና ይሰገዳል።የፈጅርን ሰላት መስጊድ ውስጥ ከህዝቡ ጋር በጋራ (ጀመአ) የሰገደ በአላህ ጥበቃ ስር እንደሚውል ነብዩ ተናግረዋል።

    • ዝሁር ሰላት 4 ረከአ ሲሆን ከዋናው ሰላት በፊት እና በኋላ ሁለት ሁለት ወይም አራት አራት ረከአ ሱና መስገድ ይወደዳል።አስር 4 ረከአ ሲሆን ከዋናው ሰላት በፊት ሁለት ሁለት እያደረጉ 4 ረከአ ሱና መስገድ ይወደዳል።መግሪብ 3 ረከ ሲሆን ኢሻ 4 ረከአ ሰላት ነው።

ከኢሻ በፊት እና በኋላ ሱና ቢሰገድ ይወደዳል። አንድ ሙስሊም ሰላት አይጠቅምም አያስፈልግም ብሎ ከተውው ከ ኢስላም ጓዙን ጠቅልሎ ይወጣል። በስንፍና እና በ እንዝህላልነት አንዴ እየስገደ አንዳንዴ የሚተወው ከሆነ ደግሞ በጣም ከባድ ማስጠንቀቂያ እና በቁር አን ወዮለት የሚል ዛቻ ስላለ አንድ ሙስሊም ሙስሊም ሊባል የሚችለው ሰላትን በወቅቱ እና ደንቡን ጠብቆ ሲሰግድ ብቻ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። በጅመዓ(መስጊድ ከህብረተሱ ጋር )ሆኖ መስገድ ብቻን ከመስገድ በ27 ደረጃ ይበልጣል።ስለዚህ አንድ ሙስሊም የአዛን ጥሪ መስማት ከቻለመስጊድ ሄዶ የመስገድ ግዴኤታ አለበት ለዚህም ነው ሰላትን የተወ ሰው በ እስልምና ምንም ነሲብ(እድል ) የለውም የሚባለው፡ ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰልም ሰላት የአይናቸው ማረፊያ እና የልባቸው መርጋጊያ ነበረች።አንድ ሰው ወደ አላህ ከሚቃረብበት አንዱ ሶላት ነው። 3ኛ ዘካን ማውጣት።ወይም ምጽዋት የመስጠት ግዴታ ነው።ምጽዋት መስጠት ማለት አንድ ሰው ከቀለቡ እና ከልብሱ ከተለያየ ወጭ ተርፎት 10 ሽ ብር ለአንድ አመት ያክል ካስቀመጠ 2.5 % ማለት 250 ብር ዘካ (ምጽዋት የመስጠት ግዴኤታ አለበት) ዘካ በትክክል ቢወጣ ኖሮ በአለም ላይ ደሃ የሚባል አይገንም ነበር። ስለዚህ ዘካ (ምጽዋት መስጠት በ እስልምና ግዴታ ነው።)ይህም ለመግለጽ እንደሞከርኩት ለአንድ አመት ተቀማጭ ገንዘብ ካለው ነው ይህ ገንዘብም የ85 ግራም ወርቅ መጠን ሲደርስ ነው። 4ኛ የረመዳን ጾም በማንኛውም ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።በሽተኛ ካልሆነ ዐምሮውን የሳተ እብድ ካልሆነ እና ሴቶች በወር አበባ ጊዜኤ ካልሆኑ እንዲሁም መንገደኛ ካልሆኑ በስተቀር በአረበኛ የቀን አቆጣጠር 9ኛ ወር ላይ የሚገኘውን 1 ወር ረመዳን ሙስሊሞች የመጾም ግዴታ አለባቸው። ጾም ብዙ ጥቅሞች አሉት ። ሰዎች ረሃብ መኖሩን ሲያውቁ ነው ለተራበ የሚያዝኑት። ጤንነትን ለመተበቅ ፍቱን መድሃኒት ነው።በረመዳን ጾም ጊዜኤ ሰደቃ )(ምጽዋት መስጠት) በጣም ይወደዳል።የመልካም ሰሪዎች ምንዳ እጥፍ ድርብ ነው የሚሆነው በዚህ ወር። ሰዎችን ወደ መጥፎ የሚጎተጉቱ የሰይጣን አለቃዎች በዚህ ወር ይታሰራሉ።ለጾመኞች ሲባል የገሃነም ደጃፎች ይዘጋሉ የጀነት በራፎች ይከፈታሉ።በአጠቃላይ መልኩ በራስ ላይ የባህሪ ለውጥ ለማምጣት የሚቻልበት ታላቅ ትምህርት ቤኤት ነው።በረመዳን ወር የባህሪ ለውጥ ለማምጣት ይቻላል ጾም ማለት ጎህ ከመቅደዱ በፊት ጀምሮ ጸሃይ እስክትጠልቅ ከምግብ እና ከመጠጥ እንዲሁም ከግብረ ስጋ ግንኙነት ራስን ማቀብ ማለት ሲሆን ምላስንም ከዛዛታ ወሬ እና ከውሸት ከሃሜት መቆጠብ የግድ ይሆናል።ምግብ እና መጠጥ መተው ብቻ ጾም ጾም አያደርገውም። ነብዩ ሙሐመድ በሃዲሳቸው ላይ በውሸት መናገር እና መስራት ያላቆመ ሰው ምግብ እና መጠጥ ማቆሙ ብቻ ዋጋ እንደሌለው ተናግረዋል።ስለዚህ ምላስም ከመጥፎ ንግግር ከሃሜት ከውሸት መጾም አለበት፡፤አይንም መትፊ ነገር ከማየት ጆሮም መጥፎ ነገር እና ዛዛታ ወሬ ሙዚቃ ከመስማት መታቀብ አለበት። 5ኛው ሃጅ ማድረግ ሲሆን ይህም ለቻለ ሰው ብቻነው።ይህም ማለት የሃጅን ስነ ሥር ዓት ለማሟላት መካ አድርሶ የሚያመጣው ገንዘብ ያለው ሰው እና እሱ ደርሶ እስኪመጣ ቤተሰቦቹ እንዳይቸግራቸው ለነሱ የሚተውላቸው ትርፍ ገንዘብ ባለው ሰው ላይ ሃጅ በሂወቱ አንዴኤ ግዴኤታ ይሆናል።ይህን እየቻለ ሃጅ ሳያደርግ ከሞተ ከተጠያቂነት አያመልጥም። የሃጅ ስነ ስር አት ስብስብ ሁሉም ነገ የትንሳኤ ቀን አላህ ፊት የሚሰበሰብበትን ሁኔኤታ የሚያስታውስ ከ4 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በየአመቱ የሚሰበሰብበት ታላቅ ኢስላማዊ ስብስብ ነው።ሃጅ አደረገ እንዲባል እና ሃጅ እከሌእ እንዲሉኝ ብሎ ሳይሆን ከዛዛታ ወሬኤ ከአጉል ሰባይ እና ተግባር ተቆጥቦ ሃጅ ያደረገ ሰው እናቱ እንደወለደችው ሕጻን ሆኖ ወንጀሉ ይማርለታል። እንግዲህሃዲስ የተወለድ ህጻን ምንም አይነት ወንጀል የለበትም ማለት ነው።ይህ ግን የሰውን ገንዘብ የበላን አይጨምርም የሰው ገንዘብ የወሰደ ለባለቤቱ እስካልመለሰ ድረስ በኢስላም ይቅርታ አይደረግለትም።ምክንያቱም የግለሰብ መብት ስለሆነ በዚህ ምድር እንኳ ሳይከፍል ቢሞት የትንሳኤ ቀን ከመልካም ስራው የከፍላል።መልካም ስራ ከሌለው ገንዘብ የበላበትን ሰው ወንጀል ይሸከማል። ሃጅ ሁለት ፎጣ የሚእስሉ ነጭ ልብሶችን ለወንዶች ካለ ውስጥ ሱሪ የሚለበስበት እና ሁሉም ሰ እራቁትን እንደተፈጠረ እራቁቱን ወደሚቀጥለው አለም እንደሚሄድ የሚያስገነዝቡ ነገሮ/በሃጅ ቦታ ሃብታሙ ከደሃው ዶክተሩ ከገበረው የማይለይበት ሁሉም ወንድ ነጭ ልብስ ለብሶ በአረፋ ላይ የሚሰበሰብበት ሁኔኤታ አለ።አንድ ሰው የሃጅን ግዴታ ተወጣ የሚባለው አረፋ ላይ መዋል ሲችል ነው።ሴቶች የሰውነታቸውን ቅርጽ የማያሳይ ማንኛውም አይነት ልብስ መልበስ ይፈቀድላቸዋል።

   ትክክል ተናግሬኤ ከሆነ ከላህ ነው።የገለጽኳቸው ነገሮች ትክክል ካልሆእኑ ደግሞ ከነፍሴ እና ከሸይጣን ነው።እውነታውን አላህ የበለጠ ያውቀዋል።

መለጠፊያ:Link FA

መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA